Saturday, August 2, 2014

አቡነ ዘዮሐንስ ጻድቅ

 


          =>ኢትዮዽያዊው ጻድቅ የተወለዱት በ13ኛው መቶ ክ/ዘመን መጨረሻ አካባቢ ሲሆን ሃገረ ሙላዳቸው ሸዋ (መርሃ ቤቴ) ነው:: ወላጆቻቸው ዘካርያስና ሶፍያ እግዚአብሔርን የሚፈሩ: እመ ብርሃንን የሚወዱና ለነዳያን የሚራሩ ነ...በሩ::

+ደጉ ዘካርያስ መስፍን ሲሆን እርሱ በሌለበት የሸዋ ገዢ ሊያገባት በመሞከሩ ቅዱስ ገብርኤል ቀስፎታል:: ሕዝቡ ገዢነቱን ለዘካርያስ ሰጥተውታል:: ከቆይታ በሁዋላም ድንግል ማርያም የተባረከ ፍሬ ሰጠቻቸው:: ስሙን "ዮሐንስ" አሉት:: በሒደት ግን ዘዮሐንስ (የዮሐንስ) ተብሏል::

+ቅዱሱ ዘዮሐንስ እስከ 7 ዓመቱ ድረስ በእናቱ እቅፍ ቆይቶ ወደ ትምሕርት ገብቷል:: ጸጋ እግዚአብሔር ጠርቶታልና በአጭር ጊዜ ብሉይ ከሐዲስ ጠነቀቀ:: አደን ይወድ ነበርና ሊያድን ሲወጣ 'ብርሕት ደመና' ድንገት ነጥቃ ከኢትዮዽያ (ሽዋ) ወደ ኢየሩሳሌም (ጐልጐታ) አደረሰችው::

+ደስ ብሎት ቅዱሳት መካናትን ተሳልሞ ደመናዋ ወደ ሃገሩ መለሰችው:: ከጥቂት ጊዜ በሁዋላም ከሰማይ ነቢዩ ኤልያስና መጥምቁ ወርደው ባረኩትና "ክፍልህ ከእኛ ጋር እንዲሆን መንን" አሉት::

+ዘዮሐንስ ወላቹንና ቤተ ክርስቲያንን እያገለገለ (ዲቁና ነበረውና) 25 ዓመት ሞላው:: ያን ጊዜ ወላጆቹ "እንዳርህ" ቢሉት "የለም! አይሆንም" አላቸው:: አርጅተው ነበርናስ ለእነርሱ ዕረፍት ጸለየ:: ፈጣሪም ሰምቶታልና 2ቱም በክብር ተከታትለው ዐረፉ::

+ሕዝቡ በወላጆቹ ፈንታ "እንሹምሕ" ቢሉት "እንቢ" ብሎ ወርቁን: ብሩን: ርስቱን: ቤቱን ሁሉ ለነዳያን አካፍሎ ወደ ደብረ ሊባኖስ ገባ:: ጊዜው አቡነ ተክለ ሃይማኖት ባረፉ በ50 ዓመት አካባቢ ሲሆን አባ ሕዝቅያስ አበ ምኔት ነበሩ:: (ከዚህ በሁዋላ አንቱ እያልን እንቀጥል)

+አባ ዘዮሐንስ ለ7 ዓመታት ገዳሙን ረድተው መነኮሱ:: እንደ ልማዱ ደመና ነጥቆ ወስዷቸው ከኢየሩሳሌሙ ሊቀ ዻዻሳት ቅስና ተቀብለዋልና በደብረ ሊባኖስ ለ25 ዓመታት አገለገሉ:: ቤተ መቅደሱን በመዓልት 7 ጊዜ በሌሊት 7 ጊዜ ያጥኑ: እልፍ እልፍ ይሰግዱ: ተግተው ይጸልዩ: ይታዘዙም ነበር::

+ከዚያም በፈጣሪ ትዕዛዝ በትግራይና በሌሎቹ የሃገራችን ክፍሎች ወንጌልን ሰብከዋል:: እድሜአቸው 70 በሆነ ጊዜ ወደ ጌታ መቃብር (ጐልጐታ) ሔደው ተሳልመው በእርሱ (በጌታ) ትዕዛዝ ወደ ደራ (ጣና ዳር) ተመለሱ::

+በአካባቢውም ገብርኤልና መስቀል ክብራ የሚባሉ ደጋግ ባለ ትዳሮች ነበሩና በእንግድነት ከቤታቸው አደሩ:: ቤቱ በቅጽበት በበረከት ሞላ:: እነርሱም የጻድቁን አምላክ አመሰገኑ::

+ቀጥሎም በመስቀል ክብራ መሪነት ጻድቁ ዘዮሐንስ ወደ ክብራን ገብርኤል ደሴት ገቡ:: (በነገራችን ላይ ደሴቱ ክብራን የተባለ መስቀል ክብራ በምትሰኘው ደግ ሴት ስም ነው:: እርሷና ባሏ ገብርኤል የተቀደሱ ሰዎች ነበሩና)

+ጻድቁ አቡነ ዘዮሐንስ ወደ ደሴቶቹ (ክብራንና እንጦንስ ኢየሱስ) እንደ ገቡ ደሴቶቹ በግማሹ የስውራን ቤት: እኩሉ ደግሞ የጣዖት (ዘንዶ) አምላኪዎች መኖሪያ ነበር:: ጻድቁ ክብራን ገብርኤልንና እንጦንስ ኢየሱስን የመሠረቱት በ1315 ዓ/ም አካባቢ በዐፄ ዓምደ ፅዮን ዘመን ነው:: በአካባቢው ዘንዶ ይመለክ ነበርና ያንን በጸሎታቸው አጥፍተው ሕዝቡን አጥምቀዋል::

+በዚያም ገዳሙን የወንድና የሴት ብለው ከፈሉ:: የወንዶች ክብራን ሲሆን ሴት አይገባበትም:: አበ ምኔቱም ራሳቸው ጻድቁ ነበሩ:: የሴቶች እንጦንስ ኢየሱስ ከካህናት በቀር ወንድ አይገባበትም:: እመ ምኔቷም እናታችን ቅድስት ክብራ (መስቀል ክብራ) ሆነች::

+ጻድቁ አቡነ ዘዮሐንስ በክብራን ለ35 ዓመታት ተጋድለዋል:: ለጸሎት ከመቆማቸው ብዛት እግራቸው አብጦ: ቆሳስሎ ነበር:: የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዘወትር ይገለጽላቸው: ያነጋግራቸውም

ነበር::

+እጅግ ድንቅ የሆኑ ተአምራትን ሠርተው: ለወንጌል እንደሚገባ ኑረው: በተወለዱ በ105 ዓመታቸው  ዐርፈዋል:: ጌታችንም በስማቸው ለተማጸነና ገዳማቸውን ለሳመ የምሕረት ቃል ኪዳን ገብቶላቸዋል:: ልደታቸው ደግሞ ሕዳር 13 ቀን ይከበራል:: ገዳማቸው (ክብራን ገብርኤልና እንጦንስ ኢየሱስ) ድንቅ ነውና እንድታዩት ተጋብዛቹሃል::

Thursday, February 6, 2014

ቅዱሳን ጻድቃን አባቶች እና የሰማእታትን ክብር


         በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን::
 ‘’ክብር ለሚገባው ክብር ስጡ’’ ሮሜ 13፡7
ቅዱሳን ጻድቃን አባቶች እና የሰማእታትን ክብርመስጠት እንዳለብን አጭር መልዕክት ቃል ኪዳን ማለት በሁለት ወገኖች መካካል የሚደረግ ስምምነት፤ማሐላ፤ኑዛዜ ማለት ነው፡፡በዚህ ቃል መሰረት እግዚአብሔር ከፍቅሩ ብዛት የተነሳ በህይወት ዘመናቸው ሁሉ ራሳቸውን ለእርሱ አሳልፈው የሰጡትን መስቀሉን ተሸክመው ለኖሩ እና ካገለገሉ ቅዱሳን ጋር የማይሻር፤ የማይለወጥለ፤ የማይረሳ፤የማያረጅ ህያውና ዘለዓለማዊ የሆነ ቃል ኪዳን እንደገባላቸው መጽሐፍ ቅዱስ እንዲህ ሲል ይገልጸዋል፡፡‹‹ኪዳነ ተካየድኩ ምስለ ህሩያንየ - ከመረጥኩት ጋር ቃል ኪዳኔን አደረግሁ››መዝ 88፡3 እግዚአብሔር አምላክ ከወደደው ጋር ቃል ኪዳን እንደሚያደርግ የማይለወጥ መሆኑንንም አረጋግጦ ሲናገር ‹‹ኪዳኔን አላረክስም ከከንፈሬ የወጣውን አልወጥም››በማለት በግልጽ ይነግረናል፡፡
እግዚአብሔር አምላክ ለሰጠው ቃል ኪዳን ሞት ሊገድበው አይችልም፡፡ ብዙ ጊዜ ቅዱሳን በአጸደ ሥጋ ያማልዳሉ ብለን ስንናገር ከመጽሐፍ ቅዱስ ውጪ ሆነን አይደለም፡፡ሲጀመር አንድ ነዋሪ ወይም ዜጋ ዜግነታዊ መብቱ የሚጠበቅለት ግዴታውን መወጣት ሲችል ብቻ ነው፡፡እንደዚሁ አንድ ሰው በቅዱሳን ምልጃ መጠቀም የሚችለው በቅዱሳኑ አማላጅነት ማመን ሲችል ብቻ ነው፡፡ነገር ግን ቅድስት ቤተክርስቲያን ልጆቿ እንዳይጠፉ ዜጋ ለሆነውም ላልሆነውም የቅዱሳኑን አማላጅነት ዘወትር ትሰብካለች ፡፡
ቅዱሳን ከእረፍተ ሞታቸው በኋላ እንደቀደመው በአጸደ ስጋ እያሉ ሲያደርጉ እንደነበረው የመጾም ፤የመስገድ ፤ ልዬ ልዬ መከራዎችን መቀበል ባይኖርባቸውም አስቀድመው ባደረጉት ተጋድሎ በተሰጣቸውን የማማለድ ጸጋ አምነው ስማቸውን የሚጠሩ ሰዎች እንደሚድኑበት እንዲህ ተብሎ ነው የተጻው ቆላ 2፡5 ‹‹በስጋ ምንም እንኳ ብርቅ በመንፈስ ከእናንተ ጋር ነኝ ›› ሐዋሪያው በስጋ ምንም እንኳን ቢለይ በመንፈስ ከእነርሱ የማይረቀው ለምንድነው የሚለውን ማስተዋል ይኖርብናል፡፡ይህም የሚያስረዳን ቅዱሳን ከእረፍታቸው በኋላ ከእኛ የማይርቁ መሆኑን ነው የሚያሳየን፡፡ አንዲህም ተብሎ ተጽፏል ‹‹ኤልሳዕ ሞቶ ቀበሩትም ከሞዓብም አደጋ ጣዬች በየዓመቱ ወደ ሀገሩ ይገቡ ነበር፡፡ ሰዎችም አንድ ሰው ሲቀብሩ አደጋ ጣዬች አዬ ሬሳውንም በኤልሳዕ መቃብር ጣሉት የኤልሳዕንም አጥንት በነካ ጊዜ ሰውዬው ድኖ በእግሩ ቆመ ››2 ነገስት 13፡20 ይህ ቃል መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የለም እንደማይባል እርገጠኛ ነኝ፡፡እንደው ስንፍና ይዞአቸው ካልሆነ፡፡
ሌላው በቅዱሳን ስም ዝክር እያሉ መደገስ መብላት ኦርቶዶክሰ ተዋህዶ ሃይማኖት ተከታዮች ይወዳሉ በምክንያት ነው የሚበሉት ይላሉ እንዲህ ተብሎ ነው በታላቁ መጽሐፍ ቅዱስ የተጻፈው ለስም አጠራሩ ክብር ምስጋና ይግባውና መድሐኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የወዳጆቹን የጻድቃን ስም ለሚጠሩ በማይታበይና በማያልፈው ህያው ቃሉ እንዲህ ይላል ‹‹ነቢይን በነብይ ስም የሚቀበል የነብዩን ዋጋ ይወስዳል ፤ጻድቅንም በጻድቅ ስም የሚቀበል የጻድቁን ዋጋ ይወስዳል፤ ማንም ከእነዚህ ከታናናሾቹ ለአንዱ ቀዝቃዛ ጽዋ ውሃ ብቻ በደቀ መዝሙር ስም የሚያጠጣ እውነት እላችኃለው ዋጋው አይጠፋበትም›› ማቴ 10፡41-42
ታናናሾቹ የተባሉት ይኸውም በስጋዊ ኑሮአቸው የሌላውን እጅ ጠብቀው ለሚኖሩ ወገኖች ብቻ ሳይሆን በስጋዊ ኑሮ በልጽገው ለሚገኙት ሁሉ የሚሰጠው ነገር ቢያጣ እንኳ በነቢያና በጻድቃን ስም ‹‹ ስለ አምላከ ጻድቃን አምላከ ነቢያት›› ብሎ የጻድቅን ወይም የነብይን ስም ከክርስቶስ ጋር አስተባብሮ ጠርቶ ቀዝቃዛ ውሃ እንኳ ቢሰጥ ዋጋው እንደማይጠፋበት መድሐኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተናገረው፡፡የዚህንም ዋጋ ታላቅነት ሲናገር የነብዩን የጻድቁን ዋጋ ይወስዳል በማለት እስከ ምን ድረስ እንደሆነ ዋጋው ተገልጸል፡፡
የቅዱሳን ስም በመጥራት የሚደረገው መንፈሳዊ ስራ ጊዜያዊና ለተወሰነ ጊዜ ብቻ የሚቆይ ሳይሆን የማይቋረጥ መሆኑን ክቡር ዳዊት በመዝ 111/112፡6 የጻድቅ መታሰቢያ ለዘለዓለም ይኖራል: በማለት ዘላለማዊ መሆኑንም ተናግሯል፡፡ እንዲሁም የጻድቅ መታሰቢያ ለበረከት ነው ምሳ 10፡17
ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ምጽዋት፣ዝክር እና ሌሎችንም ስራዎች በቅዱሳን ስም የምታደርገው ክርስቶስ ለወዳጆቹ የገባውን ቃል ኪዳን ይዛና እግዚአብሔር ያዘዘውን የወደደው መሆኑን አውቃ ነው፡፡ስለ አምላከ ቅዱስ ጴጥሮስ፤ ስለ አምላከ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ፤ስለ አምላከ ሰማእት ቅድስት አርሴማ ….. እያለች ስማቸውን ከአምላካችን ስም ጋር አስተባብራ የምትጠራው ከባለቤቱ ተምራ ነው፡፡ ቅዱሳን ራሳቸው የእግዚአብሔርን ስም የሚጠሩት በፊት የነበሩ ቅዱሳንን ስም በማንሳት ነበር፡፡ ኤልያስ ፈጣሪውን ሲጠራ የአብርሃም የይሳቅ የያዕቆብ አምላክ ሆይ እያለ እንደነበር መጽሐፍ ቅዱስ ይነግረና ፡፡ኤልሳዕ ደግሞ የኤልያስ አምላክ እያለ ይጠራ ነበር፡፡
እንዲህ እንደ ኤልያስ በዘመናቸው ከእነርሱ በፊት የነበሩ ቅዱሳንን የሚከብሩ እነርሱ ደግሞ በተተኪው ትውልድ በመልካም ስማቸው ይዘከራሉ፡፡ መታሰቢያቸውም በኢሳ 56፣4-7 “እግዚአብሔር ሰንበቴን ስለሚጠብቁ ደስ የሚለኝንም ነገር ለሚመርጡ ቃል ኪዳኔንም ስለሚይዙ ጃንደረቦች እንዲህ ይላልና፡- በቤቴና በቅጥሬ ውስጥ ከወንዶችና ከሴቶች ልጆች ይልቅ የሚበልጥ መታሰቢያና ስም እሰጣችኃለሁ የማይጠፋ የዘለዓለም ስም እሰጣችኃለሁ አለ “ የማይጠፋ ስም “ /ይሰመርበት/ ምልጃ የእግዚአብሔር ትዕዛዝና ፈቃድ ነውን? አዎ አንዳንድ ሰዎች ራሳችን በቀጥታ እንጸልያለን እንጂ አማላጅ መፈለግ መንገድ ማብዛት ነው ይላሉ ይህ ድፍረት ነው:: መጽሐፍ ቅዱሳዊ አይደለም ዘፍ 20፡1-7 መመልከት እንችላለን አቤሜሌክን አብርሃም እንዲጸልይለት ራሱ እግዚአብሔር እንደነገረው እንመለከታለን፡፡እንዲሁም ኢዮ 42፡7-9 ባሪያዬ ኢዮብ ስለ እናንተ ይጸልያል ያለው እግዚአብሔር ነው እንዲሁም ቅዱስ ጳውሎስ በእኛ የማታረቅን አኖረ፡፡እንግዲህ እግዚአብሔር በእኛ እንደሚማለድ ስለ ክርስቶስ መልክተኞች ነን 2ኛ ቆሮ 5፡19-20 ታዲያ መናፍቃን ይህ ሁሉ ማስረጃ እያለ ለምን ይክዳሉ ከተባለ እንዲህ ተብሎ ነው የተጻፈው በመጨረሻው ዘመን እንደገዛ ምኞታቸውና አሳባቸው ለክህደት እንዲመቻቸው አድርገው መጽሐፍትን የሚያጣምሙ ክፉዎች እንደሚመጡና እንደሚያስቱ ብዙዎችም ከዚህ የተነሳ ሃይማኖታቸውን ይለውጣሉ እናንተ ግን ልጆቼ ሆይ አስቀድማችሁ እወቁ ተብሏል፡፡በመሆኑም ‹‹አይበጃችሁምና ከአባቶቻችሁ አምላክ ከእግዚአብሔር ጋር አትዋጉ ››2ኛ ዜና መዋ 13፡12 አዎ አትዋጉ ክብር ለሚገባው ክብር መስጠት ያስተማረን እግዚአብሔር ነውና አላውቅም አስተምሩን ሌላ ነገር ነው ቅዱሳንን መስደብ መዝለፍ ግን ሐጢያት ነው፡፡ምክንያቱም በቅዱሳን አማላጅነት እንኳን ባያምኑ መጽሐፍ ቅዱስ እናትና አባትህን አክብር ይላል እናም ቅዱሳን እናቶቻችን ቅዱሳን አባቶቻችንን ልናከብር ይገባል፡፡እርግጠኛ ነኝ ማናችንም ወላጅ እናታችንን ወይም ወላጅ አባታችንን አንድ ሰው ከመሬት ተነስቶ ቢሰድብብን ወይም ቢመታብን ዝም እንል ይሆን? ቅዱሳን እናቶቻችን ቅዱሳን አባቶቻችንን ከዚህም በላይ ናቸውና አይ አላከብርም የሚል ካለ መጽሐፍ ቅዱስ እንዲህ ይለናል “ እነዚህ ግን ለመጠመድና ለመጥፋት በፍጥረታቸው እንደተወለዱ አዕምሮ እንደሌላቸው እንስሶች ሆነው በማያውቁት ነገር/ባልገባቸው/ እየተሳደቡ በጥፋታቸው ይጠፋሉ የአመጻቸውን ደመወዝም ይቀበላሉ“ 2 ጴጥ 2፣12 እኛ ግን ሐዋሪያው ቅዱስ ጳውሎስ በ 2 ጢሞ 3፣17 ላይ እንደገለጸው ከልጅነት ጀምሮ በተማርነው ትምህርት ጸንተን ስንገኝ የቅዱሳኑን በረከት ተካፋይ እንሆናለን፡፡ መጽሐፍ ቅዱስን የማያውቁ ይቃወማሉ ይህ ግን መድሐኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መጽሐፍትንና የእግዚአብሔርን ሀይል አታውቁምና ትስታላችሁ ማቴ 5፡22-29 ብሎ እናውቃለን እያሉ ይስቱ የነበሩትን ሰዶቃውያኑን ከገሰጻቸው ተግሳፅ ተካፋዮች የእነርሱን እርሾ ተቀብለው ይስታሉ፡፡ ቅድስት ቤተክርስቲያንም የጌታችንን ትምህርት አስተማረች እንጂ የስድብ ቃልን አላስተማረችም፡፡ ይሁ 1፣8-10 “እነዚህ ሰዎች ደግሞ እያለሙ ስጋቸውን ያረክሳሉ ጌትነትንም ይጥላሉ ስልጣን ያላቸውንም ይሳደባሉ፡፡የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ግን ከዲያብሎስ ጋር በተከራከረ ጊዜ ስለ ሙሴ ስጋ ሲነጋገር ጌታ ይገስጽህ አለው እንጂ የስድብን ፍርድ ሊናገረው አልደፈረም እነዚህ ግን የማያውቁትን ሁሉ ይሳደባሉ “ ግን ግን አንድ ጥያቄ ላንሳ ? አለም ለበሽታዎች ቀን እየሰየመች በዓል ብላ ታከብራለች ታዲያ መጽሐፍ ቅዱስን አብነት አድርገው ቃን ኪዳኑን የፈጸሙ ቅዱሳን እንደምን አይከበሩ፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ይቆየን
አቅራቢ ገዛኸኝ ፋንታሁን ዘአርሴማ 

Thursday, November 28, 2013

ትምህርተ ጦም በሊቃውንት





በዚህ ጽሑፍ ጦምን አስመልክቶ የቅዱሳን አባቶችን አስተምህሮ እንመለከታለን
 
አንድ የገዳም አበምኔት  አንድ ወቅት አባ ጳይመን የሚባሉትን አባት “እግዚአብሔርን መፍራት እንዴት ገንዘቤ ማድረግ ይቻለኛል” ብለው  ይጠይቋቸዋል፡፡ እሳቸውም ሲመልሱ “እንዴት ሰው በላመና በጣፈጠ መብልና መጠጥ ሆዱን እየሞላ እግዚአብሔርን መፍራት ገንዘቡ ሊያደርግ ይችላል? ስለዚህም ጦም እግዚአብሔርን ወደመፍራት ይመራል፡፡ የጦም የመጨረሻ ግቡ እግዚአብሔርን ወደመፍራት ማምጣት  ነው”  ብለው ይመልሱላቸዋል፡፡
 
አንድ ወቅት አንድ ጠዋሚ በጦም ወቅት ማልዶ ይርበዋል፡፡ እናም ከሦስት ሰዓት በፊት ላለመመገብ ከፍላጎቱ ጋር ይሟገታል፡፡ ሦስት ሰዓትም ሲሆን እንደምንም ብሎ እስከ ስድስት ሰዓት ሊቆይ ይወስናል፡፡ ስድስት ሰዓት ደርሶ ሊመገብ ማዕዱን በቆረሰ ጊዜ እንደገና ለራሱ እስከ ዘጠኝ ሰዓት ልቆይ ብሎ በመናገር ምግቡን ከመመገብ ይከለከላል፡፡ ዘጠኝ ሰዓት ላይ ጸሎቱን አድርሶ ሊመገብ ሲል ሰይጣን ልክ እንደጭስ ከሰውነቱ ሲወጣ ታየው ወዲያው ረሃቡ ጠፋ፡፡
 
እየጦምክ ነውን? ለተራበ አብላ ፣ለተጠማም አጠጣ፣ ሕመምተኞችን ጎብኝ፣ የታሰሩትን ጠይቅ፣ በመከራ ላሉት እራራላቸው፣ በጭንቀት ወድቀው የሚያለቅሱትን አጽናናቸው፣ ርኅሩኅ፣ ትሑት፣የዋህ፣ ሰላማዊ፣ አዛኝ፣ይቅር ባይ፣ እውነተኛ እና ታማኝ ሁን፡፡ እንዲህ ከሆንክ እግዚአብሔር ጦምህን ይቀበልልሃል፡፡ ስለንስሐም ብዙ የንስሐ ፍሬን ይሰጥሃል፡፡ ጦም ለነፍስ ምግብ ነው፡፡
 ቁጣ መቼም ቢሆን የሚመከር አይደለም፤በተለይ በጦም ሰዓት ከቁጣ መራቅ ተገቢ ነው፡፡ ትሕትናንና ፣የዋሃትን ገንዘብህ አድርግ፤ክፉ ፈቃዶችንና አሳቦችን ተቃወማቸው፤ ራስህን መርምር በየእለቱ ወይም በሳምንት ውስጥ ምን መልካም እንደሠራህ አእምሮህን ጠይቀው፡፡ እንዲሁም ምን ስሕተትን ፈጽመህ እንደነበርና ስሕተትሕን ደግመህ እንዳትፈጽም የመፍትሔህ እርምጃዎች ምን ሊሆኑ እንዲገባቸው አሰላስል፡፡ ጦምህ እንዲህ ሊሆን ይገባዋልና፡፡
ምግብ ሰውነትን እንደሚያሰባ እንዲሁ ጦም ነፍስን ከሥጋ አስተሳሰብ ተላቃ ወደ ላይ በመነጠቅ ሰማያዊ ነገሮችን ለመመርመርና ከምድራዊ ደስታ ይልቅ እጅግ ግሩም የሆነ ደስታን ለማግኘት ጥንካሬን ይሰጣታል፡፡
 አርባ ቀን ሙሉ ከምግብ ተከልክዬ ጦምኩ አትበለኝ፡፡ ይህንና ያንን አልበላሁም ወይንም ከአፌ አልገባም አትበለኝ፡፡ እኔ ይህንን ካንተ አልሻም፣ ነገር ግን ከቁጣ ርቀህ ታጋሽ መሆንህን አሳየኝ፤ ከጭካኔህ ተመልሰህ አዛኝ ወደመሆን እንደመጣህ አሳየኝ፡፡ ነገር ግን ቁጣ የሞላብህ ከሆነ ስለምን ሥጋህን በጦም በከንቱ ትጎስማታለህ ? ሰዎችን ሁሉ የምትጠላና ስስታም ከሆንክ ለአንተ ከምግብ ተከልክለህ ውሃ ብቻ መጠጣትህ ምን ትርፍ ያመጣልሃል?
ጦም እጅግ ግሩም የሆነ ነገር ነው፡፡ ኃጢአታችንን እንደማይጠቅም አረም ከውስጣችን ይነቅለዋል፡፡  እውነተኛው የጽድቅ ተክልም  በውስጣችን ልክ እንደ አበባ እንዲያብብ ይረዳዋል፡፡ (ቅዱስ ባሲልዮስ)
ጸሎት፣ ጦም ፣ትጋህ ሌሊት እና ሌሎችም አንድ ክርስቲያን የሚተገብራቸው ክርስቲያናዊ ተግባራት ምንም መልካሞች ቢሆኑ የክርስቲያናዊ ሕይወት ግቦች ግን አይደሉም፡፡ ነገር ግን ወደ ትክክለኛው ክርስቲያናዊ ሕይወት ለመድረስ የሚያገለግሉን መንፈሳዊ ትጥቆች ናቸው፡፡ትክክለኛው የክርስቲያን ግብ መንፈስ ቅዱስ በእርሱ ሰውነት ውስጥ ሥራ እንዲሠራ በመፍቀድ የመንፈስ ቅዱስ ፍሬዎችን አፍርቶ መገኘት ነው፡፡በዚህ ምድር የመንፈስ ቅዱስ ፍሬዎች ማፍራት እስካልቻልን ድረስ የእግዚአብሔርን መንግሥት መውረስ አይቻለንም፡፡ (ቅዱስ ሱራፊ)
የአዋጅ ጦም ሲገባ መንፈሳዊ የበጋ ወራቱ እንደገባ ልብ እንበል፡፡ ስለዚህም የጦር መሳሪያችንን እንወለውለው  ከእርሻቸው አዝመራውን የሚሰበሰቡትም ገበሬዎች ማጭዳቸውን ይሳሉ፤ ነጋዴዎችም በከንቱ ገንዘባቸውን ከማባከን ይከልከሉ፣ መንገደኞችም ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ለመግባት መንገዳቸውን ያቅኑ፡፡ ወደ እግዚአብሔር መንግሥት የምትወስደው ጎዳና ቀጭንና ጠባብ ናትና በጥንቃቄ እያስተዋላችሁ ተጓዙ፡፡
እንዲያው በልማድ ሰዎች እንደሚፈጽሙት ዓይነት ጦም ትጦሙ ዘንድ አልመክራችሁም፡፡ ነገር ግን ከምግብ ስለምንከለከልባት ጦም ብቻ ሳይሆን ከኃጢአት ስለምንከለከልባት  እውነተኛይቱ ስለሆነችው ጦም እጽፍላችኋለሁ፡፡ ጦም በባሕርይዋ በሕግ ካልተመራች  ለሚተገበሩዋት ሰዎች ዋጋን አታሰጥም፡፡ ስለዚህም ጦምን ለመጦም ስንዘጋጅ የጦም ዘውድ የሆነውን ነገር መዘንጋት የለብንም፡፡ ስለዚህ ስለምን ያ በእግዚአብሔር ቤተመቅደስ ደጅ ሆኖ ጸሎቱን ያደረሰው ፈሪሳዊ ከእግዚአብሔር ዘንድ ስለጦሙ አንዳች ዋጋ ሳያገኝ በባዶው እጁ እንደተመለሰ መረዳት ተቀዳሚ ተግባራችን ሊሆን ይገባዋል (ሉቃ. ፲፰፥፱-፲፬(18፡9-14))፡፡ ቀራጩ አልጦመም ነገር ግን ጸሎቱ ተሰምቶለታል፡፡ ጦም ሌሎች አባሪ የሚሆኑ መልካም ሥራዎች ካልታከሉበት በቀር ልክ እንደዚኛው ፈሪሳዊ ዋጋ አያሰጠንም፡፡
ጦም ማለት መድኃኒት ማለት ናት፡፡ እንደ ሌሎቹ መድኃኒቶች ሁሉ ጦምን እንዴት እንደሚጠቀምበት የሚያውቅ ሰው ዋጋ ያገኝበታል፡፡ በጥበብ ላልተጠቀመበት ሰው ግን የማይረባና የማይጠቅም ይሆንበታል፡፡ ከጦም የሚገኘው ክብር ከምግብ በመከልከላችን ምክንያት የምናገኘው ብቻ አይደለም፡፡ ከኃጢአት ሥራዎችም ፈጽመን በመከልከላችን ምክንያት የምናገኘው ክብር ጭምር ነው ፡፡ ጦም ሰይጣን ወደ እኛ እንዳይቀርብ እንደጋሻ የሚያገልግለን መሣሪያ ነው፡፡ ነገር ግን በጦም ሰዓት ኃጢአትን ፈቅደን የምንሠራት ከሆነ ሰይጣን አጥሩን ጥሶ እንዲገባና በእኛ ላይ እንዲሠለጥን ምክንያት እየሆንነው ነው፡፡ ጦማችን ከምግብ በመከልከል ብቻ የተወሰነ ከሆነ ጦምን እናስነቅፋታለን፡፡
እየጦምክ ነውን ? መጦምህን በሥራህ ገልጠህ አሳየኝ፡፡ ድሃው እርዳታህን ፈልጎ እንደሆነ ቸርነትን አድርግለት፡፡ ጠላት ያደረግኸውን ካየኸው ከእርሱ ጋር ፈጥነህ ታረቅ፡፡ ጓደኛህ ተሳክቶለት ካየኸው በእርሱ ላይ ቅናት አይደርብህ፡፡ አፍህ ብቻ አይጡም ዐይንህም ጆሮህም እግርህም እጅህም የሰውነትህ ሕዋሳቶች ሁሉ ክፉ ከማድረግ ይጡሙ፡፡
እጆችህ ከዝርፊያና ከሕግ ውጪ ለመክበር ሲባል ትርፍን ከማጋበስ ይጡሙ፡፡ እግሮችህ የኃጢአት ሥራን ለመፈፀም ከመፋጠን ይጡሙ፡፡ ዐይኖችህም ውጫዊ በሆነ ውበት ምክንያት ከመቅበዝበዝ ይጡሙ፡፡ የሚታዩ ነገሮች ለዐይን ምግቦች ናቸው፡፡ ነገር ግን ከእግዚአብሔር ሕግ ጋር የሚጣረሱ ምልከታዎች ጦምን ያፈርሳሉ፡፡ነፍስንም እንድትነዋወጥ ያደርጉአታል፡፡ የምናያቸውን ነገሮች ከእግዚአብሔር ሕግ ጋር የሚስማሙ ከሆኑ ጦማችንን ያስጌጡዋታል፡፡ በጦም ምክንያት በጦም ሰዓት መመገብ የተከለከሉትን ምግቦች መመገብ የሚያስነቅፍ ከሆነ ፤ እንዴት ታዲያ በዐይናችን እንድንመለከተው በሕግ የተከለከልነውን ነገር መመልከታችን ይበልጥ አያስነቅፈን ? ምግብን ከመብላት ተከልክለሃልን? እንዲሁ ለሰውነትህ ጎጂ የሆኑ ነገሮችን በዐይንህም በጆሮህም ከመመገብ ተከልከል፡፡ ጆሮ የምትጦመው ለኃጢአት ከሚጋብዙ ክፉ ወሬዎችና ሐሜትን ከመስማት ነው፡፡ “ሐሰተኛ ወሬን አትቀበል ሐሰተኛ ምስክርም ትሆን ዘንድ ከኃጢአተኛ ጋር እጅህን አታንሣ፡፡”እንዲል(ዘጸአ.፳፫፥፩(23፡1))
አፍህም ከከንቱ ንግግር ይጡም ፡፡ ከአሣና በጦም ሰዓት መመገብ ከተከለከልናቸው የፍስክ ምግቦች ተከልክለን ወንድሞቻችንንና እኅቶቻችንን በክፉ ቃላችን ሕሊናቸውን የምናቆስልና በሐሜት ሥጋቸውን የምንበላ ከሆነ ከጦማችን ምን ዋጋን እናገኛለን? ክፉ ተናጋሪ የወንድሙን አካል ያቆስላል ሥጋውንም ይበላል፡፡ ስለዚህም ቅዱስ ጳውሎስ ይህን አስመልክቶ  እጅግ የሚያስደነግጥ ንግግርን ተናገረ “ሕግ ሁሉ በአንድ ቃል ይፈጸማልና እርሱም፡- ባልንጀራህም እንደ ራስህ ውደድ  የሚል ነው፡፡ ነገር ግን እርስ በእርሳችሁ ብትነካከሱና ብትበላሉ እርስ በእርሳችሁ እንዳትጠፋፉ ተጠንቀቁ፡፡(ገላ.፭፥፲፭(5፡15))ብሎ አስጠነቀቀን፡፡
ስለታሙ የሐሜት ጥርስህ የሚያርፈው በወንድምህ ሥጋ ላይ ሳይሆን ነፍስ ላይ ነው፡፡ በዚህም ጥርስህ ወንድምህን በእጅጉ ትጎዳዋለህ፡፡ እንዲህ በማድረግህ አንተም እርሱንም ሌሎችንም ብዙ ሺህ ጊዜ ትጎዳቸዋለህ፡፡ በሐሜትህ አንተን የሚሰማህ ባልንጀራህ የሐሜት ተባባሪ ይሆናል፡፡ በዚህም ምክንያት እርሱንም በደለኛ ታደርገዋለህ፡፡ እርሱም በእርሱ ላይ ከነገሠበት ኃጢአት የተነሣ ለሌላ ለወዳጁ ምን መርጦ ማውራት እንዳለበት ሳያውቅ ከሐሜተኞች ጎራ ይቀላቀላል፡፡እንዲህ ዓይነት ሰው ጻድቅ ልንለው እንችላለንን? እንዲህ ዓይነት ሰው  በመጦሙ ትልቅ የጽድቅ ሥራን እንደፈጸመ ቆጥሮ ይኩራራል፡፡ ሰዎችን ወደ ኃጢአት እየመራ ትልቅ ሥራን እንደሠራ ሰው ራሱን በከንቱ ያስኮፍሳል፡፡ ከዚህ ጎን ለጎን ሊታይ የሚገባው ትልቁ ቁም ነገር ስለቤተክርስቲያን ጥቅም ሲባል የእንዲህ ዓይነቱን ሰው ንግግር ከመስማት መከልከል እንደሚገባ ነው፡፡ ምክንያቱም የዚህ ሐሜተኛ ወሬ እርሱን ብቻ ኃጢአተኛ የሚያሰኝ ጉዳይ ሳይሆን ቤተክርስቲያንንም ጭምር የሚያሰድብ ነውና፡፡
ስለዚህ በጦም ሰዓታችሁ ጊዜም ይሁን አይሁን  ሦስት ነገሮችን በሕሊናችሁ ትይዙ ዘንድ እመክራችኋለሁ፡፡ እነርሱም ክፉ ከመናገር መከልከልን፣ ማንንም ሰው እንደጠላት ከማየት መቆጠብንና እንደልምድ አድርጋችሁ ከያዛችሁት መሐላ ትርቁ ዘንድ እመክራቸኋለሁ፡፡
በአጨዳ ላይ ያለ ገበሬ እህሉን ከእርሻው ላይ በአንዴ እንዳይሰበስብ ነገር ግን ጥቂት በጥቂት እንዲሰበስብ እኛም እነዚህን ምክሮች ተግባራዊ በማድረግ በዚህ የጦም  ወቅት ልንለማመዳቸው እና መልካም ልምዶቻችን ልናደርጋቸው ይገባናል፡፡ እንዲህም በማድረጋችን በቀላሉ መንፈሳዊ ጥበብን ገንዘባችን ማድረግ ይቻለናል፡፡ በዚህም ዓለም ሳለን መልካም ተስፋ ያለውን አዝመራ እናፈራለን፡፡በሚመጣውም ዓለም በክርስቶስ ፊት ያለፍርሃት በደስታ ተሞልተን እንድንቆም ይረዱናል፡፡ ለእግዚአብሔር መንግሥት የሚያበቃንን ጸጋ አግኝተን የክብሩ ወራሾች ያድርገን፤ ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ ክብር ምስጋና ይሁን ዛሬም ዘወትርም እስከዘላለሙ አሜን፡፡
 ጦም የጤንነት እናት፣ የፍቅር እኅት፣ የትሕትና ወዳጅ ናት፡፡ ሕመሞች አብዛኛውን ጊዜ ያለቅጥ ከመመገብ የሚመነጩ ናቸው፡፡ (ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ)
ከምግባራት ሁሉ ታላቁ ጸሎት ነው ነገር ግን የእርሱ መሠረቱ ጦም ነው፡፡የምንጦምበት ምክንያት ርኩስ የሆነውን የሰይጣንን መንፈስ በነፍሳችን ውስጥ እንዳያድር ለመጠበቅ ነው፡፡ ሥጋችንን ለጦም ባስገዛነው ጊዜ ነፍሳችን ነፃነትን፤ ጥንካሬን ሰላምን ፣ንጽሕናን እንዲሁም እውቀትን ለመለየት እንድትበቃ ትሆናለች፡፡ (ጻድቁ ዮሐንስ ዘክሮስታንድ)
እውነተኛ ጦዋሚ ራሱን ከክፉ ምግባራት የከለከለ፤ ከንቱ የሆኑ ንግግሮችን ከመናገር የተቆጠበ፣ ሐሰትን የማይናገር፣ ሐሜተኛ ያልሆነ፣ በማንም ላይ የማይፈርድ፣ሽንገላን የማይወድና እኒህንም ከመሰሉ ነገሮች ራሱን የተጠበቀ ፣የማይቆጣ፣ የማይበሳጭ ፣ተንኮለኛ ያልሆነ ፣ ቂመኛ ያልሆነና፣ እነዚህን ከመሳሰሉ ክፋቶች ሁሉ የራቀ ሰው ነው፡፡
ሕሊናህ ኃጢአትን  ከማሰብ ይጡም፡ አእምሮህም ኃጢአትን ከማስታወስ ይከልከል፡፡ ክፉን ከመመኘት ሁሉ ጡም፡፡ ዐይኖችህ ከንቱ የሆኑ ነገሮችን ከመመልከት፣ ጆሮህም ከንቱ ከሆኑ ዘፈኖችና ከሐሜተኞች ሹክሹክታዎች ጠብቅ፡፡ አንደበትህ ከሐሜት፣ በሌላው ላይ ከመፍረድ ፣ከስድብ፣ ከውሸት ፣ከማታለል፣ከሽንገላ ንግግሮች እንዲሁም ከማይጠቅሙና አጸያፊ ከሆኑ  ቃላት ይጡሙ፡፡ እጆችህም ሰውን ከመግደልና የሌላውን ንብረት ከመዝረፍ ይጡሙ፡፡ እግሮችህም ኃጢአትን ለመፈጸም ከመሄድ ይጡሙ፡፡ ከክፉ ተመለስ መልካምንም ፈጽም፡፡ (ቅዱስ ኤፍሬም)
 ጦም ምን እንደሚያደርግ ትመለከታለህን? ሕመምን ይፈውሳል ፣አጋንንትን ያስወጣል፣ ክፉ አሳቦችን ከአእምሮ ያስወግዳቸዋል፣ ልብንም ንጹሕ ያደርጋታል፡፡ አንድ ሰው በክፉ መንፈስ የተያዘ ቢሆን  እንዲህ ዐይነት መንፈስ በጦምና በጸሎት እንደሚወጣ ያስተውል፡፡ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ “ይህ ዓይነት ግን ከጸሎትና ከጦም በቀር አይወጣም” እንዳለው (ማቴ. ፲፯፥፳፩(17፡21)) (ቅዱስ ቲክሆን)
የአርባ ቀን ጦም የሥጋ ፍትወታትን ይገድላቸዋል፣ቁጣንና ብስጭትን ከሰውነታችን ያስወግዳቸዋል፣  ከሆዳምነት ከሚመነጩ የትኞቹም ነገሮች ሁሉ ነፃ ያወጣናል፡፡ በበጋ ወራት ፀሐይ ከነሙሉ ኃይሉዋ እንድትወጣና ምድርንም በሙቀቱዋ እንደምታግል በላዩዋም የበቀሉ አትክልቶችን እንደምታደርቅ፤ ከሰሜን የሚነፍሰውም ነፋስ የደረቁትን ሳሮች እንደሚጠርጋቸው፤  እንዲሁ በጦም ወቅትም አብዝቶ በመመገብ የበቀሉትን የሥጋ ፍትወታት ይወገዳሉ፡፡ (ቅዱስ አትናቴዎስ)
ቅዱሳን ጠዋሚዎች ጽኑ ወደሆነው የጦም ሥርዓት የገቡት ወዲያው አይደለም፡፡  በጥቂት ምግብ ወደ መጥገብ የመጡት ቀስ በቀስ ነው፡፡ እነዚህ ቅዱሳን ኃጢአትን ፈጽመው አያውቋትም፡፡ ሁልጊዜ ለመልካም ሥራ እንደተፋጠኑ ነው፡፡ በእነርሱ ዘንድ ሕመም አይታወቅም እድሜአቸውም  ከሰው ሁሉ በተለየ የረዘመ ነው፡፡ (ቅዱስ አግናጢዎስ)
ጦም  የሰውን እድሜ አያሳጥርም ፣ ቅዱስ ቄርሎስ ዘአንኮራይት በ108 እድሜው አረፈ፡፡ ቅዱስ እንጦስም 105 ዓመት ሙሉ ኖሮአል፡፡ ቅዱስ መቃርስ ዘእስክንድሪያ የኖረበት እድሜ 100 ዓመት ነበር ፡፡ (ቅዱስ አውግስጢኖስ)
አርባውን ቀን መጦምን ቸል አትበሉ፡፡ ምክንያቱም ክርስቶስን የምንመስልበት ሕይወት ከዚህ ጦም እናገኛለንና፡፡ (ቅዱስ እንጦስ) 
ወስብሐት ለእግዚአብሔር ለዘበቅዱሳኒሁ ይሴባሕ ይእዜኒ ወዘልፈኒ ወለዓለም ዓለም አሜን፡፡ ወአሜን ለይኩን ለይኩን፡፡   

Friday, September 13, 2013

saint moses the ethiopian

      Abraham, the disciple of Abba Agathon, questioned Abba Poemen, saying, “How do the demons fight against me?” Abba Poemen said to him, “The demons fight against you? They do not fight against us at all as long as we are doing our own will. For our own wills become the demons, and it is these which attack us in order that we may fulfill them. But if you want to see who the demons really fight against, it is against [Abba] Moses and those who are like him.


Abba Moses (Hymns and the 7 instructions)

”Seven instructions which Abba Moses sent to Abba Poemen. He who puts them into practice will escape all punishment and will live in peace, whether he dwells in the desert or in the midst of brethren.

1. The monk must die to his neighbor and never judge him at all, in any way whatever.

2. The monk must die to everything before leaving the body, in order not to harm anyone.

3. If the monk does not think in his heart that he is a sinner, God will not hear him. The brother said, ‘What does that mean, to think in his heart that he is a sinner?’ Then the old man said, ‘When someone is occupied with his own faults, he does not see those of his neighbor.’

4. If a man’s deeds are not in harmony with his prayer, he labors in vain. The brother said, ‘What is this harmony between practice and prayer?’ The old man said, ‘We should no longer do those things against which we pray. For when a man gives up his own will, then God is reconciled with him and accepts his prayers.’

The brother asked, ‘In all the affliction which the monk gives himself, what helps him?’ The old man said, ‘It is written, “God is our refuge and strength, a very present help in trouble.”’ (Ps-46.i)

5. The old man was asked, ‘What is the good of the fasts and watchings which a man imposes on himself?’ and he replied, ‘They make the soul humble. For it is written, “Consider my affliction and my trouble, and forgive all my sins.” (Ps.25.18) So if the soul gives itself all this hardship, God will have mercy on it.’

6. The old man was asked, ‘What should a man do in all the temptations and evil thoughts that come upon him?’ The old man said to him, ‘He should weep and implore the goodness of God to come to his aid, and he will obtain peace if he prays with discernment. For it is written, “With the Lord on my side I do not fear. What can man do to me?”’ (Ps. i 18.6)

7. A brother asked the old man, ‘Here is a man who beats his servant because of a fault he has committed; what will the servant say?’ The old man said, ‘If the servant is good, he should say, “Forgive me, I have sinned.”’ The brother said to him, ‘Nothing else?’ The old man said, ‘No, for from the moment he takes upon himself responsibility for the affair and says, “I have sinned,” immediately the Lord will have mercy on him.

The aim in all these things is not to judge one’s neighbor. For truly, when the hand of the Lord caused all the first-born in the land of Egypt to die, no house was without its dead.’

The brother said, ‘What does that mean?’ The old man said, ‘If we are on the watch to see our own faults, we shall not see those of our neighbor. It is folly for a man who has a dead person in his house to leave him there and go to weep over his neighbor’s dead.

To die to one’s neighbor is this: To bear your own faults and not to pay attention to anyone else wondering whether they are good or bad. Do no harm to anyone, do not think anything bad in your heart towards anyone, do not scorn the man who does evil, do not put confidence in him who does wrong to his neighbor, do not rejoice with him who injures his neighbor. This is what dying to one’s neighbor means. Do not rail against anyone, but rather say, “God knows each one.”

Do not agree with him who slanders, do not rejoice at his slander and do not hate him who slanders his neighbor. This is what it means not to judge. Do not have hostile feelings towards anyone and do not let dislike dominate your heart; do not hate him who hates his neighbor. This is what peace is: Encourage yourself with this thought, “Affliction lasts but a short time, while peace is for ever, by the grace of God the Word. Amen.” ‘

Friday, September 6, 2013

ቅዱስ ሩፋኤል ጦቢት እና ጦቢያ

ስለዚህ እንግዶችን መቀበል አንርሳ፡፡ በዚህም ምክንያት አንዳንዶች ሳያውቁ የመላእክትን እንግድነት ተቀብለዋልና፡፡ ዕብ. 13.1-2 ፡፡
በየዓመቱ ጳጉሜ 3 የቅዱስ ሩፋኤል መልአክ መታሰቢያ ነው ፡፡ ቅዱስ ሩፋኤል የጦቢትን ዓይን ያበራና ወለተ ራጉኤልን ተቆራኝቷት ከነበረው ጋኔን ያላቀቃት መሆኑ በመጽሐፈ ጦቢት በስፋት ተገልጿል፡፡
ጦቢት በፋርስ ንጉሥ በስልምናሶር ዘመን የተማረከ ከነገደ ንፍታሌም የተወለደ ጽኑዕ እሥራኤላዊ ነው፡፡ እግዚአብሔር በስልምናሶር ፊት የመወደድን ግርማና ባለሟልነትን ስለ ሰጠው አለቃ አድርጎ ሾሞት ነበር፡፡ ለወገኖቹ ምጽዋት በመስጠት ሕገ ርትዕን በመሥራት የተጋ ሰው ነበር፡፡ ሐና የምትባል ሚስት አግብቶ አንድ ልጅ ወልዷል፡፡ ስልምናሶር ሞቶ ሰናክሬም በነገሠ ጊዜ ከሹመቱ ስለሻረው ደግሞ ወደ ምድያም መሔድ አልቻለም፡፡
ሣራ ወለተ ራጉኤል ከፍተኛ ችግር ደርሶባት ነበር፡፡ ችግሯም ሕፃናት ወልጄ ቤት ንብረት ይዤ እኖራለሁ በማለት ባል አገባች ነገር ግን በዚች ሴት አስማንድዮስ የሚባል ጋኔን አድሮ ያገባችውን ሰው ገደለባት ሌላም ባል ብታገባ ሞተባት እንደዚህ እየሆነ በጠቅላላ ሰባት ድረስ ያሉትን ባሎችን ገደለባት፡፡

የራጉኤል ልጅ ሣራ በዚህ ሁኔታ በኀዘን ተውጣ ስትኖር በነበረበት ጊዜ ጦቢት ሸምግሎ ስለ ነበር ልጁ ጦብያን ጠርቶ በዚህ ዓለም እስካለ ድረስ ሊሠራው የሚገባውን መንፈሳዊ ሥራ እንዲሠራ በጥብቅ ከመከረው በኋላ በመጨረሻ ልጄ እኔ ሳልሞት የኑሮ ጓደኛህን ፈልግ፣ ስትፈልግም ዕወቅበት፣ እኛ የአብርሃም የይስሐቅና የያዕቆብ ዘሮች ነን ስለዚህ ከእነርሱ ወገን የሆነችውን እንድታገባ ከዚህም ሌላ ከገባኤል ዘንድ በአደራ ያስቀመጥኩት ገንዘብ አለና እኔ በሕይወት እያለሁ ብታመጣው የተሻለ ነው አለው፡፡
ጦብያም ያባቱን ምክር ሁሉ በጽሞና ካዳመጠ በኋላ ‹አባባ የነገርከኝን ነገር ሁሉ በተቻለኝ መጠን እፈጽማለሁ ግን ከገባኤል ጋር ስላለው ገንዘብ እንዴት ለማምጣት እችላለሁ? ሀገሩን አላውቀውም› አለው፡፡ በዚህ ጊዜ ነገሩ አሳሳቢ ሆኖ ስላገኘው ጦቢት ልጁ ጦብያን ‹አብሮህ የሚሄድ ሰው እስቲ ፈልግ ምናልባት አብሮ የሚሄድ ጓደኛ ታገኝ ይሆናል ደመወዝም ሰጥተን ቢሆን ካንተ ጋር የሚሄድ አንድ ሰው ግድ ያስፈልግሃልና ሂድ ሰው ፈልግ› አለው፡፡
ጦቢት ስንቃቸውን አስይዞ ጦብያ ቅዱስ ሩፋኤል ሸኛቸው
አብሮት የሚሄደው ሰው ለመፈለግም ቢሄድ አንድ መልካም ጐበዝ አገኘ ይኸውም መልአኩ ቅዱስ ሩፋኤል ነው፡፡ጦብያ ግን መልአኩ ቅዱስ ሩፋኤል መሆኑን ፈጽሞ አላወቀም ነበር፡፡ ይሁን እንጂ ጦብያ መልአኩን ሰው መስሎ እንዳገኘው ‹የሜዶን ክፍል ወደ ምትሆነውና ራጌስ ወደ ምትባለው ሀገር ከእኔ ጋር ለመሄድ ትችላለህን የድካምህን ዋጋ የጠየቅኸውን ያህል እሰጥሃለሁ› ሲል ጠየቀው ቅዱስ ሩፋኤልም ‹እሺ ካንተ ጋር ለመሄድ ፈቃኛ ነኝ መንገዱንም ሆነ ሀገሩን በሚገባ አውቀዋለሁ ከገባኤል ቤት ብዙ ጊዜ ኑሬአለሁና› አለው፡፡
ከዚህ በኋላ ጦብያ በል ከአባቴ ጋር ላስተዋውቅህ ብሎ ወደ አባቱ ወስዶ አስተዋወቀው ከእኔ ጋር የሚሄደው ሰው ይህ ነው በማለት ካስተዋወቀው በኋላ ጦቢትም ከወዴት እንደ መጣ ማን ተብሎ እንደሚጠራ ጠየቀው፡፡ መልአኩ ቅዱስ ሩፋኤልም የታላቅ ወንድምህ ወገን ከመሆንም ሌላ ስሜም አዛርያስ ይባላል አለው፡፡ ጦቢ. 5.12 ፡፡ ጦቢትም የወንድሙ ዘመድ መሆኑን ከሰማ በኋላ ‹አንተስ ወንድሜ ነህ በል የልጄ የጦብያን ነገር አደራ ከሀገር ወጥቶ አያውቅምና እንዳይደነግጥ ደኅና አድርገህ እንድትይዝልኝ› ብሎ ስንቃቸውን አስይዞ ሸኛቸው፡፡
አዛርያስ /ቅዱስ ሩፋኤል/ በመንገድ ይመራው ነበር፡፡ በዚህም ቅዱስ ሩፋኤል ‹መራኄ ፍኖት› /መንገድ መሪ/ ይባላል፡፡ እነርሱ ሲሄዱ ውለው ማታ ጤግሮስ ከተባለው ታላቅ ወንዝ ደረሱና ከዚያም ለማደር ወሰኑ፡፡ በዚህ ጊዜ ከድካሙ ጽናት የተነሣ ጦብያ ሊታጠብ ወደ ወንዙ ወረደና ልብሱን አውልቆ መታጠብ ሲጀምር አንድ ዓሣ ሊውጠው  ከባሕር ወጣ፡፡ ወዲያውም መልአኩ ቅዱስ ሩፋኤል ጦብያን ያዘው ፤ ዓሣውን እንዳትለቀው አለው ፤ ጦቢያም ከዓሳው ጋር ግብ ግብ ገጥሞ እየጐተተ ወደ የብስ አወጣው ፡፡ከዚህ በኋላ ቅዱስ ሩፋኤል ጦብያን እንዲህ ሲል አዘዘው፡፡  ዓሣውን እረደው ጉበቱንና ሐሞቱን ተጠንቅቀህ ያዘው ሌላውን ግን ጠብሰን እንበላዋለን አለው፡፡
ጦብያም መልአኩ እንዳዘዘው ዓሣውን አርዶ ሐሞቱንና ጉበቱን ያዘ
ጦብያም መልአኩ እንዳዘዘው ዓሣውን አርዶ ሐሞቱንና ጉበቱን ያዘ፣ ሌላውን ሥጋውን ግን ጠብሰው ራታቸው አደረጉት፡፡ ጦብያም ያንን የዓሣውን ጉበትና ሐሞት ለምን እንደሚያገለግል ለመረዳት ‹ይህን ያዘው ያልከኝ ለምንድን ነው?› ሲል ጠየቀው ቅዱስ ሩፋኤልም ጋኔን ያደረበት ሰው ሲገኝ ይህንን ከዕጣን ጋር ቢያጤሱበት ጋኔኑ ይለቃል ሲል መለሰለት፣፡
በዚህ ሁኔታ አንድ ባንድ ሲነጋገሩ ከቆዩ በኋላ መልአኩ ቅዱስ ሩፋኤል ጦብያን ‹ዛሬ ከራጉኤል ቤት እናድራለን፡፡ እርሱ ዘመድህ ነው፡፡ የእርሱም ልጅ ሣራ የምትባል ቆንጆ ልጅ አለችው፡፡ እሷን ለሚስትነት ይሰጥህ ዘንድ ለራጉኤል እነግርልሃለሁ› አለው፡፡
ጦብያም ‹ያች ልጅ ከዚህ በፊት ሰባት ሰዎች እንዳገቧትና ሰባቱም ባገቧት ሌሊት ደርቀው /ሞተው/ እንደሚያድሩ ሰምቻለሁ፡፡ ስለዚህ እኔ ላባቴና ለእናቴ አንድ ልጅ ነኝ እርስዋን አግብቼ ከዚህ በፊት እንዳገቧት ሰዎች እኔም የሞትኩ እንደሆነ አባቴንና እናቴን የሚረዳቸው የለም ቢሞቱም የሚቀብራቸው አያገኙምና እፈራለሁ› አለው፡፡ መልአኩ ቅዱስ ሩፋኤል ግን  ‹አባትህ ከዘመዶችህ ወገን ካልሆኑ በስተቀር ሌላ ሴት እንዳታገባ ሲል የነገረህን ረሳኸውን? በል ሰባት ባሎቿ ሙተውባታል ስለምትለው እኔ መድኃኒቱን አሳይሃለሁ ፤ አይዞህ አትፍራ አትሞትም የዓሣውን ሐሞትና ጉበቱን ለምን መሰለህ ያዘው ያልኩህ ? እንግዲህ ሐሞቱንና ጉበቱን ከዕጣን ጋር  ጨምረህ ስታጤስበት በሣራ አድሮ የነበረው አስማንድዮስ የተባለው ጋኔን ወጥቶ ይሄዳል ፈጽሞም ወደ እርሷ በገባህም ጊዜ ሁለታችሁ ይቅር ባይ ወደ ሆነው እግዚአብሔር ጸልዩ እርሷም የተዘጋጀች ናት፡፡ ከእኛ ጋርም ወደ ሀገርህ ይዘናት እንሄዳለን› አለው፡፡ ጦብያም ይህንን ቃል በሰማ ጊዜ ደስ አለውና ከእርሷ በስተቀር ሌላ እንዳያገባ በሙሉ አሳቡ ወሰነ፡፡
ከዚህ በኋላ ወደ ራጉኤል ቤት እንደ ደረሱ ሣራ በደስታ ተቀበለቻቸው የሣራ አባትም ጦብያን ገና እንዳለው ሚስቱ አድናን ‹ይህ ልጅ የእኔ ዘመድ ጦቢትን ይመስላል› አላት ከዚያም ጋር አያይዞ ‹ልጆች ከየት ሀገር መጣችሁ?› አላቸው፡፡ እነሱም ‹ከነነዌ ሀገር ነው የመጣን› አሉት፡፡ ‹ከዚያም ሀገር ጦቢት የሚባል ወንድም ነበረኝ ታውቁት ይሆን?› ሲል ጠየቃቸው፡፡ በዚህ ጊዜ ጦቢያ አባቱን ሲጠራለት ‹እናውቀዋለን፡፡ እኔም ራሴ የጦቢት ልጅ ነኝ› አለው፡፡ ከዚያ በኋላ ራጉኤል ‹የወንድሜ ልጅ ነህን?› ብለ እቅፍ አድርጐ ሳመው፡፡ አድናም ሳመችውና ሁሉም ተያይዘው የናፍቆት ልቅሶ ተላቀሱ፡፡ ከወንድሙ እንደ መጡም ሲገነዘብ በግ አርዶ በጥሩ ሁኔታ ጋበዛቸው፡፡
ራትም ከበሉ በኋላ ጦብያ ቅዱስ ሩፋኤል በመንገድ የነገረውን በልቡ ሲያወጣ ሲያወርድ ስለ ዋለ  ቅዱስ ሩፋኤልን ያንን በመንገድ የነገርከኝን አሁን ፈጽምልኝ ሲለው ሰምቶ ስለ ልጅቷ መሆኑን ስለ ገባው ራጉኤል ጦብያን ‹ልጄ ይህች ልጅ ላንተ የምትገባ ናት ሰጥቸሃለሁ አይዞህ አትጠራጠር አሁንም ብላ ጠጣ ለዛሬም ደስ ይበልህ አለውና ሣራ ካለችበት የጫጉላ ቤት አግብተው ዘጉት፡፡ ጦብያም ሣራን በይ እኅቴ ኑሮዋችን እንዲቃናልንና ጋብቻችን እንዲባረክልን አስቀድመን ወደ ፈጣሪያችን ጸሎት እናድርግ› አላትና አብረው ጸሎት ካደረጉ በኋላ ያንን የያዘውንና የዓሣ ጉበትና ሐሞት ከዕጣን ጋር ጨምሮ ቢያጤስበት በሣራ አድሮ ባሎችዋን ይገድልባት የነበረው አስማንድዮስ የተባለው ጋኔን ከሣራ ለቆ ወጥቶ ሄደ ሁለተኛም ሊመለስ አልቻለም፡፡ እነርሱም በሰላምና በጤና አደሩ፡፡ የጦብያንና የሣራን ጋብቻ የባረከ ቅዱስ ሩፋኤል ስለሆነ ‹መልአከ ከብካብ› ይባላል፡፡
ከዚያ በኋላ የጤንነታቸውን ነገር ሲረዱ የሰርጉ ቀን የሚሆን የ14 ቀን በዓል እስኪፈጸም ድረስ ጦብያ ወደ ሀገሬ እሄዳለሁ ብሎ እንዳያውከው በማለት አማለው፡፡
ጦብያ የዓሣውን ሐሞትና ጉበቱን ይዞ ስለ ነበር የአባቱን ዓይን ቀባው ወዲያውም ዓይኖቹ ተከፈቱ
የ14 ቀን በዓለ መርዓ ከተፈጸመ በኋላ ግን ጥሬ ገንዘብና የከብት ስጦታ አድርጐ መርቆ ወደ ሀገሩ ሰደደው፡፡ ወላጆቹ ጦቢትና አድና ግን በመዘግየቱ ልጃችን ምን አግኝቶት ይሆን? እያሉ ለጊዜው ሳያዝኑ አልቀሩም፡፡ ከጥቂት ቀናት በኋላ ሚስቱንና ግመሎቹን ይዞ ሲመጣ በክብርና በደስታ ተቀበሉት፡፡ የጦብያ አባት ጦቢትም ልጅህ መጣ ሲሉት ዓይነ ሥውር ስለ ነበር እርሱን እቀበላለሁ ሲል ስለ ወደቀ ወዲያው ጦብያ የዓሣውን ሐሞትና ጉበቱን ይዞ ስለ ነበር የአባቱን ዓይን ቀባው ወዲያውም ዓይኖቹ ተከፈቱ፡፡
 የቅዱሳንን ጸሎት ከሚያሳርጉ ከሰባቱ ሊቃነ መላእክት አንዱ እኔ ሩፋኤል
ነኝ› ሲል ገለጠላቸው፡፡ እነርሱም ወድቀው የአክብሮት ስግደት ሰገዱለ
በመጨረሻም ከጦብያ ጋር ሄዶ የነበረው  መልአኩ ቅዱስ ሩፋኤልን የድካሙን ዋጋ ገንዘብ ለመስጠት ጠሩት እርሱ ግን ጦቢትንና ጦብያን ‹ፈጣሪያችሁን አመስግኑ እናንተ እስከ ዛሬ ድረስ ከየት እንደመጣሁ ማን እንደ ሆንኩ አላወቃችሁኝም፡፡ የእግዚአብሔር ምሥጢር ግን በክብር ሊገለጥ ይገባል እንጂ ሊሰውሩት ስለማይገባ የእኔን ተፈጥሮና ስም ልነግራችሁ እፈልጋለሁ ተፈጥሮዬ መልአክ ነኝ፣ ሥራዬም የቅዱሳንን ጸሎት ከሚያሳርጉ ከሰባቱ ሊቃነ መላእክት አንዱ እኔ ሩፋኤል ነኝ› ሲል ገለጠላቸው፡፡ እነርሱም ወድቀው የአክብሮት ስግደት ሰገዱለት፡፡ የአባቶቻቸውን አምላክ እግዚአብሔርንም አመሰገኑት፡፡ /መጽ. ጦቢት/፡፡
ስለዚህ እንግዶችን መቀበል አንርሳ፡፡ በዚህም ምክንያት አንዳንዶች ሳያውቁ የመላእክትን እንግድነት ተቀብለዋልና፡፡ ዕብ. 13.1-2 ፡፡
ጦቢት ከእህሉ ከፍሎ ለተራበ የሚያበላ ከልብሱ ለተራቆተ ሰው የሚያለብስ እግዚአብሔርን ዘወትር የሚያመሰግን ለወገኖቹ የሚራራ አሥራት በኩራት የሚያወጣ ሰው ነበር፡፡ በመሆኑም በሥራው ሁሉ እንዲረዳው በችግሩ ጊዜ እንዲያጸናው ቅዱስ ሩፋኤል ተልኮለታል፡፡ እኛም በሕይወታችን የጐደለብንን ነገር እንዲሞላልን ጐዳናችንን እንዲያስተካክልልን ከክፉ ጋኔን እንዲጠብቀን አምላክ ቅዱስ ሩፋኤል ተለመነን ቅዱስ ሩፋኤልንም አማልደን ማለትን ገንዘብ እናድርግ፡፡
ጳጉሜ የዘመን መሸጋገሪያ እንደ ሆነች ዕለተ ምጽአትም ወደ እግዚአብሔር መንግሥት የምንሸጋገርባት ስለሆነች ከወዲሁ የቅዱስ ሩፋኤልን የመታሰቢያ በዓሉን ስናከብር በአማላጅነቱ ከቅዱሳን ኅብረት እንዲደምረን በንስሐ ታጥበን ደጅ ልንጠና ይገባል፡፡ 
የቅዱስ ሩፋኤል ልመናው ይደረግልን በረከቱ ይደርብን፡፡ አሜን፡፡

Sunday, September 1, 2013

st Mamas the great martyr ቅዱስ ማማስ


Martyr Mamas of Caesarea in Cappadocia (275), and his parents, Martyrs Theodotus and Rufina
September 2

He began his life in the cruellest of circumstances: both of his parents were imprisoned for their faith in Christ. First his father, Theodotus, died in prison, then his mother, Rufina, died shortly after his birth, so the infant was left alone in prison beside the bodies of his parents.

But an angel appeared to the widow Ammia, telling her to go to the prison and rescue the child. Ammia obtained the city governor's permission to bury the parents and bring the child home.

He was called Mamas because he was mute until the age of five and his first word was `Mama'. Despite his late beginning, he showed unusual intelligence and, having been brought up in piety, soon openly proclaimed his Christian faith.

When he was only fifteen years old he was arrested and brought before the Emperor Aurelian. The Emperor, perhaps seeking to spare the boy, told him to deny Christ only with his lips, and the State would not concern itself with his heart.

Mamas replied `I shall not deny my God and King Jesus Christ either in my heart or with my lips.' He was sent to be tortured, but miraculously escaped and lived in the mountains near Caesarea.

There he lived in solitude and prayer and befriended many wild beasts. In time, he was discovered by the persecutors and stabbed to death with a trident by a pagan priest.
ምንጭ holy father

Thursday, July 4, 2013

አቡነ ተክለ ሐዋርያት ዘደብረ ጽሞና ካልዕ


  
        በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን::
  አቡነ ተክለ ሐዋርያት ዘጽሞና ካልዕ ዘያበርህ አዕፋሩ የተባሉት ደገኛ አባት ትውልድ ሀገራቸው ሸዋ ደብረ ጽሞና የሆኑት በአጼ ዘርዓያዕቆብ የነበሩ በአባ አትናቴዎስ መቃብር ላይ ሄደው አጥብቀው የጸለዩ ፯ አክሊል የወረደላቸው ጌታ ተገልጾ ከጊዮርጊስና፤ ከዮሐንስ መጥምቁ ጋር ነው ክፍልህ ያላቸው ጻድቅ ናቸው። በዚህም ሙታን የተነሱላችሁ ብዙ ተዓምር ያደረጉ ብርሃን የወረደላቸው ታላቅ ጻድቅ ናቸው። ሲጸልዩ ነፍሴ ፫ (ሦስት) ነገርን ትፈልጋለች ይሉ ነበር። 1 ከዚህ ዓለም ሀሜት መራቅን 2 ክፉ ነገር ከማየት መራቅን 3 ከንቱ ነገር ከመስማት መራቅነ እያሉ ይማጸኑ ነበር። እንዲህ እያሉ በሚጸልዩበትም ወቅት መልአኩ መጣና ወደ በረሃ ምንም ሰው ወዳሌለበት ሂድ አላቸው። እንዳላቸው ወደ ምድረ ሐጋይ በዝዋይ አድርገው አልፈው ከባሕር ውስጥ ባለ ዋሻ ገቡ። ከዚያ ገብተው ይጸልዩ ጀመር። በዚያም ብርሃን ወርዶላቸው ነፍሴ ሰውነቴን ተጸየፈች እያሉ ይጸልዩ ጀመር። በዚያን ጊዜ ጌታ ተገልጾላቸው ቃል ኪዳን ገብቶላቸዋል። ለኢትዮጵያ መኩሪያ ነህ ሲል ታሪካቸውን በብጹህ አቡነ ባስልዮስ ትዕዛዝ በዜና ቤተ ክርስቲያን ጋዜጣ በ1945 እና 1946 ዓ.ም በወጣ ታሪካቸው በስፋት ተመዝግቦአል። በመጨረሻም አባታችን አቡነ ተክለ ሐዋርያት ሕዳር 27 ቀን በክብር አርፈዋል። መላዕክትም 5 ሆነው ወርደው ቀብረዋቸዋል። መጀመሪያ በደብረ ብርሃን ተቀብረው ከ13 ዓመት በኋላ በምዕራብ ሸዋ አህጉረ ስብከት ስር በምትገኘው ወደ ደብረ ፅሙና አፅማቸው መጥተዋል።

አባታችን አቡነ ተክለሐዋርያት ከሌሎች ፃድቃን ለየት የሚያደርጋቸዉ አንድ ዓመት የታመመ ህመምተኛ ሥጋወደሙ ወስዶ (ተቀብሎ ) ከህመሙ የተነሳ አስመለሰዉ ዲያቆኑ ያስመለሰዉን በእቃ ተቀበለዉ ። ደምና መግል የተቀላቀለበት ነበር አባታቺን አቡነ ተክለሐዋርያት ሰለ ስጋወ ደሙ ክብር በእለተ አርብ ሃሞትና ሆምጣጥዉን እንደ አጠጡት የወልድን የመስቀሉን መከራ አስበዉ ፈጣሪአቸዉን ከመዉደዳቸዉ የተነሳ ያንን ያስመለሰውን ግጥም አደርገዉ ጠጡት በዘያን ጊዜ ጌታችን ወደሳቸዉ መጥቶ ወዳጄ ተክለሐዋርያት ሆይ በሰዉ ፊት እዳከበርከኝ በሰማያዊ መላአክትና በምድራወዊ ፃድቃን ሰማእታት ፊት አከብርሃለሁ ብሎ ጣቱን አንስቶ በጣቱ ፊታቸዉን በባረከዉ ግዜ ፊታቸዉ እንደ ፀሐይ አበራ በፊቱም ላይ ያለዉ የፀሐይ ብረሃን በምድር ላይ ሁሉ ታየ ።
አንድ ዶሮ በሰበት ቀን ከባለቤቱ አምለጦ መጥቶ አስጥለኝ ብሎ ለመናቸዉ አሳቸዉ የዶሮዉን ባለቤት ሰንበት ነዉ አትረደዉ ቢሉት አልሰማ ሰላላቸዉ ያላቸዉን ሸማ (ልብስ ) ሰጥተዉ ከመታረድ አድነዉታል በስእሉ ላይ አንደሜታየዉ ።
ክብር ይግባዉና የኛ አምላክ የቅዱሳንን ሥራ አይተን ሰምተን አንብበን እነሱ የሰሩትን መስራት ባንችል እንኳን ተስፋ እድንቆርጥ አልተወንም ምንም እንኳን እነሱ የተጋደሉትን ተጋድሎ መጋደል ባንችል ደካሞች ብንሆን ይልቁንም እነሱን ብንቀበል በነሱ ስም አንድ ጽዋ ቀዝቃዛ ዉሃ ብንሰጥ የነሱን ዋጋ እደሚሰጠን ቃል ገባልን አንጂ ማቴ ፲ ፬፩ አቡነ ተክለ ሐዋሪያት መድህን ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ ግንባራቸው ላይ ጸሐይ ያተመባቸው ታላቁ አባት ናቸው ቅድስት ቤተክርስቲያንም ወር በገባ በ27 አስባቸው ትውላለች፡፡ የጻድቁ በረከታቸው ይደርብን አሜን
†እንግዲህ እነዚህን የሚያህሉ ምስክሮች እንደ ደመና በዙሪያችን ካሉልን፥ እኛ ደግሞ ሸክምን ሁሉ ቶሎም የሚከበንን ኃጢአት አስወግደን፥ የእምነታችንንም ራስና ፈጻሚውን ኢየሱስን ተመልክተን፥ በፊታችን ያለውን ሩጫ በትዕግሥት እንሩጥ፤ እርሱ ነውርን ንቆ በፊቱም ስላለው ደስታ በመስቀል ታግሦ በእግዚአብሔር ዙፋን ቀኝ ተቀምጦአልና።† ዕብ. ፲፪:፩-፪
  የአባታችን አቡነ ተክለ ሐዋርያት ረድኤታቸው፣ ጸሎታቸው፣ ቃል ኪዳናቸው አማላጅነታቸው ከሁላችንም ጋር ይሁን አሜን።
አሜን†††

 ዋቢ መጽሐፍት፡-
 የኢትዮጵያ ተወላጆች ቅዱሳን ታሪክ በሊቀ ብርሃናት መርቆሬዎስ አረጋ ፲፱፻፪ ዓ.ም ገጽ ፶፩-፶፪ (51-52)
 ሽንቁሩ ሚካኤል ከሚል መጽሐፍ
ወስብሐት ለእግዚአብሔር ለዘበቅዱሳኒሁ ይሴባሕ ይእዜኒ ወዘልፈኒ ወለዓለም ዓለም አሜን፡፡ ወአሜን ለይኩን ለይኩን፡፡