Tuesday, December 8, 2015

የቅድስት አርሴማ ተአምር

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን

እነሆ ተአምር ከሰማእቷ ቅድስት አርሴማ
ገዳም።
ለሌሌች አድርሱ ይህን መስክሩ.!
እናት ማዬት ስለተሳናት ልጃቸው ብለው ሱባኤ
ለመያዝ ጎንደር ጭልጋ ወረዳ ቅድስት አርሴ ማ
ገዳም ተገኝተዋል። በገዳሙ ስርአት መሰረት ሱባኤ ይዘው ለሁለት ሳምንት ገብተዋል፣
በፀሎት እና በልመና ሳያቋርጡ የዘውትር
ናፍቆታቸውን በልመና ወደ ፈጣሪ ያሳስባሉ
ሰማእቷን እርጅኝ ይህችን አንድ
ፍሬ ህፃን ብርሃን ስጫት ለኔም ረድኤትሽ ይድረሰኝ
እያሉ ሳያቋርጡ ይፀልያሉ። በዚህ ሁኔታ ሁለት ሳምንት ተቆጠረ
በስተመጨረሻም ቀነ ቀጠሮው ደረሰ እና አንድ ቀን
እማማ በሱባኤ እያሉ ሚጡዬ ከተኛችበት ባንና
ተነሳች እና በድንጋጤ
ሁሉን አተኩራ አዬቻቸው በማደሪያው ያሉትን
አብረዋት ያሉትንም ከእንቅልፏ ተነስታ አፍጥጣ አስተዋለቻቸው ሰዎቹም
ሁለት ልብ ሆኑ ማየት አትችልም ነበርና አሁን ግን
ሁሉንም እያዬች በልጅነት ግራ መጋባት እንዲህ ብላ
አሳገራሚ ነገር ነገረቻቸው።
>> አንዲት ሴት ተነሽ ተነሽ ብላ ቀሰቀሰችኝ
ሴትዬዋ ደግሞ እንደዚህች ትመስላለች ብላ በማደሪያው ቤት ያለውን የቅድስት
አርሴማ ስዕለ አድህኖ ጠቁማ አሳዬቻቸው። ማዬት
የተሳናት ህፃን ልጅ በሰማእቷ እርዳታ ማዬት
ቻለች። ይህም ብቻ አይደለም! ህፃኗ እንዲህ ብላም
ነግራቸዋለች የቀሰቀሰቻት ይች
ሴት ብዙ ጊዜ እየታዬቻት ታናግራት እንደነበርም ነግራቸዋለች!
እማማ በሱባኤ በነበሩበት ቀናት አይኗ ለማያዬው
ህፃን
ሰማእቷ በአይነ ልቦናዋ ትገለጥላት እና ትታያት
ነበር።
አይደንቃችሁም ወዳጆቼ? የእናት ልመና ቀላል አይደለም!!!
እምነታቸው የፀና ነውና ለዛውም ፊደል ሳይቆጥሩ
በልቦናቸው
ብርሃን እየተመሩ ፈቃዱን እየፈፀሙ ይኖራሉና
እግዚአብሔር
ም ልመናቸውን ሰምቶ ይፈፅምላቸዋል! የእናቶች ፀሎት እና
ልመና ጠብ የምትል አይደለችም!! ያደለው
ቅዱሳንን ተማፅኖ
እንዲህ ቤቱ በተአምራት ይሞላል! ይባረካል
ይፈወሳል!
እኛስ??? … … እስካሁን ዶክተርን ልመና ካገር አገር
የምንባዝን ስንቶቻችን ነን? እኔ የሚገርመኝ ማን
ወደ ማን
ነበር መምጣት የሚገባው? ባለፀጋስ ማነው?
መድሀኒት
ያለውስ የት ነው? እግዚአብሔር ሁላችንም ወደ ልቦናችን
ይልሰን እና በእጃችን የያዝነውን እንቁ
እንድናስተውል ይርዳን።
እግዚአብሔር ይህንን የቅዱሳኑን ድንቅ እና በረከት
እንድናይ
የበቃን የተዘጋጀን እንድንሆን ይርዳን አሜን። የእግዚአብሔር ስሙ የተመሰገነ ይሁን አሜን!
~Like
~Comment
~Share