Sunday, November 25, 2012

ነገረ ማርያም ብሉይ ኪዳን ክፍል አንድ 2

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን
     የሴቶች ኹሉ መመኪያ  ልዑል እግዚአብሄር ሔዋንን በአርአያ በአምሳል በክብር ከአዳም እኩል አድርጎ ቢፈጥርም በሔዋን ስህተ ምክንያት ሴቶች ሁሉ የሚመኩበት ነገር አጥተው የሴትነት ክብር ተነፍጓቸው ምድረ ርስት ከመውረስ ተከልክለው ወንዶች እየተመኩባቸው ይኖሩ ነበር::ሆኖም ግን በሔዋን ምክንያት ያጡትን ክብር ዳግመኛ በቅድስት ድንግል ማርያም ተመልሶላቸዋል ከወንዶች ጋር መተካከላቸው በጉልህ ታውቋልና እመቤታችን የሴቶች ሁሉ መመኪያ ትባላለች::
     ይኸውም በብሉይ ኪዳን ዘመን የነበሩ ወንዶች ሴቶችን << ሔዋን ከእኛ ወገን ከሆነ ከአዳም ብቻ ተገኘች እንጂ አዳም ከሔዋን አልተገኘም እያሉ በሴቶች ላይ እየተመኩባቸው ይኖሩ ነበር >> በዚህም ሲያዝኑ አምስት ሺህ አምስት መቶ ዘመን ሲፈፀም አካላዊ ቃል ክርስቶስ ያለ አባት ከቅድስት ድንግል ማርያም በድንግልና ተፀንሶ በድንግልና ከተወለደ በኋላ ግን ሴቶች ሁሉ ሐዘናቸው በደስታ ተለውጦ << ሔዋን ከእናንተ ወገን ከሆነ ከአዳም ብትገኝ ከኛ ወገን ከሆነች ከቅድስት ድንግል ማርያም ሰማያዊ ንጉስ ክርስቶስ እንበለ ዘርዕ ተወልዶ የለምን >> እያሉ  የሚመኩባት ሆነዋልና እመቤታችን የሴቶች እናቶቻችን እህቶቻችን ሁሉ መመኪያቸው ናት (1ኛ ቆሮ 11*12: ገላ 4*4)
     ሊቁ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ሴቶች በድንግል ማርያም ምክንያት ስላገኙት መተካከል በመጽሐፉ ላይ <<ከመ ኢይትመካህ በእንተ ዘአውሃ ብእሲተ ዘእንበለ ብእሲት ወለደት ድንግል ብእሴ ዘእንበለ ብእሲ ከመ በሱታፌ መንክር ይትዐወቅ ዝንቱ አሐዱ ክብርቴንተ ፍጥረት>> አዳም ያለ እናት ሔዋንን ስለአስገኘ እንዳይመካ ድንግል ያለ አባት ክርስቶስን ወለደች ድንቅ በሚሆን አንድነት ይህ አንድ ፍጥረት እኩልነት ይታወቅ ዘንድ በማለት አስረድስቷል::
    በብሉይ ኪዳን ቀድሞ ወንዶች ሴቶችን ከእናንተ ወገን በሆነች በሔዋን ስሕተት ምክንያት ከርስታችን ከገነት ወጥተናል እያሉ ምክንያት በመፍጠር ሴቶችን ምድረ ርስትን አያካፍላቸውም ነበር ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ለገላትያ ሰዎች በጻፈላቸው መልእክዩ ላይ << ከክርስቶስ ጋር እንድትሆኑ ዘንድ የተጠመቃችሁ ሁሉ ክርስቶስን ለብሳችኋልና አይሁዳዊ ወይም የግሪክ ሰውየለም ባሪያ ወይም ጨዋ ሰው የለም ወንድም ሴትም የለም ሁላችሁም በክርስቶስ ኢየሱስ አንድ ሰው ናችሁና እናንተም የክርስቶስ ከሆናችሁስ እንኪያስ የ አብርሃም ዘር እንደ ተስፋው ቃል ወሾች ናችሁ>> (ገላ 3* 28)በማለት እውነተኛውን ትምህርት በማስተማር እኩልነታቸውን አጉልቶ አስተምሯል:: ሴቶችም ይህንን ትምህርት በመረዳታቸው የሰውን ዘር ሁሉ ወደ ቀደመ ቦታችን ወደቀደመ ርስታችን ወደ ቀደም ክብራችን የመለሰ ክርስቶስ ከቅድስት ድንግል ማርያም ከተወለደ ወዲህ ወንዶችን << በኛ ምክንያት ከገነት ከመንግስተ ሰማያት ብትወጡ ከኛስ ወገን ከሆነች ከቅድስት ድንግል ማርያም ጌታ ተወልዶ ርስታችሁን ገነት መንግስተ ሰማያ አግኝታችኋል የለምን>> እያሉ የሚመኩናት ህነዋል ቅድስት ድንግል ማርያም የሴቶችን ዕዳ የከፈለችላቸው መመኪያቸው ናት::
     ይህንንን ልዩ ምስጢር ሊቁ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ << ወሀሎ ላዕለ ትዝምደ አንስት ዕዳ ለትዘምድ ዕደው እስመ እማአዳም ወፃት ብእሲት እንበለ ብእሲት ወበእንተ ዝንቱ ወለደት ድንግል ብእሴ እንበለ ዘርዐ ብእሲ ከመ ትፈድዮ ለብእሲ ዕዳሃ ለሔዋን >> ለወንዶች የሚከፈለው ዕዳ በሴቶች ላይ ነበረ ያለ እናት ሔዋንተገኝታ ነበርና ለዚህም ድንግል ያለ ያለ ወንድ ዘር ክርስቶስን ወለደች ሔዋንን ብድራት ለወንዱ ትከፍለው ዘንድ በማለት ሲገልፀው::
     ሌላኛው ሊቁ ቅዱስ ያዕቆብ ዘስሩግም በሔዋን ስንፍና ምክንያት ሴቶች ያጡትን ክብር ዳግመኛ በድንግል ማርያም ምክንያት ማግኘታቸውን በስፋትና በጥልቀት ሲገልፅ (O daughters of the nation approach and learn to praise) የህዝቦች ሴቶች ልጆች ሆይ ከአባቶቻችሁ ስህተት ነፃ ያወጣችሁን ቅረቡት እርሱንም ማመስገን ተማሩ ያ ሔዋን የዘጋችውን የማይናገር አፍ አሁን በእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ተከፈተ ለእህቶቻችን ምስጋናን ለመዘመር አሮጊቷ ሴት  ሔዋን በምላሶቻችሁ ዙሪያ የዝምታን ገመድ ቋጠረች የድንግል ልጅ እስራታችሁን ፈታ ጮሃችሁ ታመሰግኑ ትዘምሩ ዘንድ ያገባችሁ ሔዋን የዝምታን መጠምጠሚያ በአፋችሁ አኖረች ግን ድንግሊቱ የተዘጋውን የምላሳችሁን በር ከፈትች እስከ አሁኑ ወገናችሁበሔዋን ምክንያት አንሶ ነበር ከእንግዲህ ወዲህ ግን ሃሌ ሉያን ለመዘመር ተመልሷል ከእናታችሁ ከሔዋን ክፋት የተነሳ ከፍርድ በታች ነበራችሁ ከእህታችሁ ከድንግል ማርያም ልጅ የተነሳ ግን ነጻ ወጣችሁ ያለ ህፍረት ምስጋናን ለማዘእም ፊታችሁን ግለጡ በልደት ለሰው ልጆች ነጻነት የሰጣችሁን ታመሰግኑ ዘንድ በማለት ድንግል ማርያም ለሰው ልጆች ነጻነት በተለይ ለሴቶች እኩልነት ያደረገችውን ድርሻ በስፋት አስተምሯል::
    ይኸውም ሔዋን ሴቶች ሁሉ ለእግዚአብሄር ምስጋና እንዳያቀርቡ የዘጋቺውን አፍ ዳግመኛ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ለእግዚአብሄር ክብር ዝማሬ እንዲያቀርቡበት ምክንያት ሆናቸዋለችና የሴቶች ሁሉ መመኪያ ተብላለች::
    የእግዚአብሔር፣ቸርነት የድንግል ማርያም አማላጅነት፣ የቅዱሳን መላእክት ተራዳኢነት፣ የጻድቃን፣ የሰማዕታት፣ የቅዱሳን ሐዋርያት፣ የቅዱሳን አበው መነኮሳት፣ የቅዱሳት አንስት፣ የደናግላንና የቅዱሳን ሁሉ ምልጃና ቃል-ኪዳናቸው ባለንበት ከሁላችን ጋር ይሁን:: ይቆየን   አነሳስቶ ያስጀመረኝ አስጀምሮ ያስጨረሰኝ የቅዱሳን አባቶቻችን አምላክ ይክበር ይመስገን አሜን፡፡
 ወስብሐት ለእግዚአብሔር ለዘበቅዱሳኒሁ ይሴባሕ ይእዜኒ ወዘልፈኒ ወለዓለም ዓለም አሜን፡፡

Wednesday, November 21, 2012

የገና ጾም - ጾመ ነቢያት

ነቢዩ ኢሳይያስ



ነቢያት ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ መወለድ፣ ወደ ግብፅ ስለ መሰደድ፣ በባሕረ ዮርዳኖስ ስለመጠመቅ፣ በትምህርተ ወንጌል ጨለማውን ዓለም ስለ ማብራቱ፣ ለሰው ልጆች ድኅነት ጸዋትወ መከራ ስለመቀበሉና ስለ መሰቀሉ፣ ስለ ትንሣኤው፣ ስለ ዕርገቱና ስለ ዳግም ምጽአቱ ትንቢት ተናግረው አላቆሙም፤ ለአዳም የተሰጠው ተስፋ ተገልጦላቸው ለተናገሩት ትንቢት ፍፃሜ እንዲያደርሳቸው ፈጣሪያቸውን ተማፀኑትም እንጂ፡፡ በየዘመናቸው «አንሥእ ኃይለከ፣ ፈኑ እዴከ፤ ኃይልህን አንሳ እጅህንም ላክ» እያሉ ጮኹ፡፡ በጾምና በጸሎት ተወስነውም ሰው የሚሆንበትን ጊዜ በቀናት፣ በሳምንታት፣ በወራትና በዓመታት ቆጠሩ፡፡ ለምሳሌ ነቢዩ ኤርምያስ ስለ ሥጋዌው ትንቢት በተናገረ በ446 ዓመት ጌታችን ከእመቤታችን ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷ ነፍስ ነስቶ ሰው ሆኗል፡፡
አባታችን አዳም እና እናታችን ሔዋን ዕፀ በለስ በመብላታቸው ምክንያት ከገነት እንደተባረሩ











ነቢያት ተስፋው በዘመናቸው ተፈጽሞ በዓይነ ሥጋ ለማየት ባይችሉም እግዚአብሔር «የማያደርገውን ይናገር የተናገረውን አያስቀር» ብለው አምነው ከወዲሁ ተደሰቱ፡፡ለዘመነ ሥጋዌ ቅርብ የነበሩት እነ ኢሳይያስ ጾሙ እንዴት መፈጸም እንዳለበትተናግረዋልም፡፡ ኢሳ 58-1፡፡

በመሆኑም በጌታ ልደት ትንቢተ ነቢያት ስለ ተፈጸመበት ይህጾም «የነቢያት ጾም» ይባላል፡፡ የወልደ እግዚአብሔርን ሰው መሆን ያስተማሩበት የሰውልጆች ተስፋ የተመሰከረበት የምሥራቹ የተነገረበት ስለሆነም «ጾመ ስብከት» ይባላል፡፡
                     ነቢዩ ኤርምያስ
ሰው በኃጢአት ቢወድቅም ፈጣሪው ሊያነሳው፤ ቢጠፋ ሊፈልገው እንደሚመጣ በተስፋ ሲጠብቀው ወልደ አምላክ ሰው መሆኑ የተረጋገጠ እውነት ነው፡፡ ስለዚህ አዳም የልደቱን ነገር በትንቢት መነፅርነት ሲመለከተው /በነቢያቱ ትምህርትና ስብከት/ በሚኖርበት ዓመተ ፍዳ የምሥጢረ ሥጋዌ  ብርሃን ከሩቅ ሲመለከተው ኖረ፡፡ ምሥጢረ ሥጋዌን በትንቢት መነፅርነት ማየቱም መከራውን እንዲቋቋመው የተስፋ ስንቅ ሆነው፡፡
ክርስቲያኖች ከእግዚአብሔር በጸጋ እንደተወለዱ በማመን ለእግዚአብሔር ያላቸውን ፍቅር ከሚገልጡባቸው ነገሮች አንዱ ጾም ነው፡፡ ጾም የፍቅር ስጦታ ከመሆኑ በተጨማሪ ታዛዥነትንና የገቡትን ቃል ኪዳን ጠባቂነትንም ማሳያ ነው፡፡ የሰው ልጅ በእግዚአብሔር አርአያ ተፈጥሯአል፡፡ ኃጢአት ሠርቶ የእግዚአብሔር አርአያነቱን ቢያጠፋውም እግዚአብሔር ግን በአርአያው ሲፈጥረው ምን ያህል እንደሚወደው ማረጋገጫ ስለነበር በኃጢአት ሲወድቅም እንደወጣ ይቅር ሳይል ሊፈልገው መጣ፡፡ እግዚአብሔር የሰውን ልጅ ሊፈልግ የመምጣቱ ተስፋ የተነገረበትንና ሱባኤ የተቆጠረበትን ዕለት ለማየት በመናፈቅ ከቀረበው መሥዋዕት አንዱ ጾም ነበር፡፡
  ጾም ሰው ለእግዚአብሔር ያለውን ፍቅር እና ታዛዥነት መግለጫና ማረጋገጫ ብቻ ሳይሆን ሲወድቁ መነሻ ከብልየት (እርጅና )መታደሻ፥ ከኃጢአት ቆሻሻ መታጠቢያ /ከንስሓ ጋር አብሮ ሲፈጸም/ ሳሙናም ነው፡፡ ሊቀ ነቢያት ሙሴ በሲና ተራራ ላይ እግዚአብሔር ወደ ነበረበት ጨለማ የገባው፣ አስፈሪውን መብረቅና ነጐድጓድ የተቋቁመው፣ ጨለማውን አልፎ የሰው ልጅ ያልሠራትን ሰማያዊ መቅደስ የተመለከተውና ወደ ዓለቱ ድንጋይ የቀረበው ራሱን ለእግዚአብሔር በጾም በመቀደስ ጭምር ነው፡፡ /የወገን ፍቅርና ለእግዚአብሔር ታዛዥነቱ እንዳለ ሆኖ/፡፡
ጾም እነዚህንና መሰል መንፈሳዊ በረከትን ስለሚያስገኝ ክርስቲያኖች ይመጣላቸው ዘንድ ይናፍቁታል፡፡ ከእነዚህ የሚናፈቁ አጽዋማት መካከል አንዱ ጾመ ነቢያት ነው፡፡ ጾመ ነቢያት የሚባለው ጾመ ገና፣ ጾመ ማርያም፣ ጾመ አዳም፣ ጾመ ፊልጶስ ተብሎ ይጠራል፡፡
 ጾመ ነቢያትም ሆነ ሌሎች አጽዋማት ሲደርሱ ክርስቲያኖች የሚደሰቱት ጾም የሥጋ ፈቃድ እንዳይሰለጥንባቸው፣ ቁስለ ሥጋን በማከም፣ ቁስለ ነፍስን ስለሚፈውስላቸው ነው፡፡  ጾም የቁስል መፈወሻ ኃይለ መዊዕም(ድል ማድረጊያ) ይሆናል፡፡ ከሥጋም ከመንፈስም ተቆራኝቶ ሰውን ወደ ጥፋት የሚወስድን ክፉ መንፈስ ለማራቅም ይጠቅማል፡፡
ጾም የሥጋን ምኞት እስከመሻቱ ቆርጦ የሚጥል፣ ለመንፈስ ልዕልና የሚያበቃውን መሳሪያ የሚያስታጥቅ ነው፡፡ ክርስቲያን ይህን መሰል መንፈሳዊ የጦር እቃ እንዳይለየው አጥብቆ ይለምናል፡፡ የጦር ልምድ እንደሌለው ወታደር ጠላቱን የሚቋቋምበት የጦር ትጥቅ ሳይዝ አውላላ ሜዳ ላይ  ባዶውን አይቆምም፡፡ መንፈሳዊ ውጊያን በሥጋዊ ጥበብ ማሸነፍ ስለማንችል ነው አበው ፍቅረ አጽዋማትን በአስተምህሮአቸውና በሕይወታቸው የሰበኩልን፡፡
ጾም እነዚህንና መሰል መንፈሳዊ በረከትን ስለሚያስገኝ ክርስቲያኖች ይመጣላቸው ዘንድ ይናፍቁታል፡፡ ከእነዚህ የሚናፈቁ አጽዋማት መካከል አንዱ ጾመ ነቢያት ነው፡፡ ጾመ ነቢያት የሚባለው ጾመ ገና፣ ጾመ ማርያም፣ ጾመ አዳም፣ ጾመ ፊልጶስ ተብሎ እንደሚጠራ መምህር ቃኘው ወልዴ ጾምና ምጽዋት በተሰኘው መጽሐፋቸው ገልጠውታል፡፡
 ጾመ ነቢያት ለአዳም የተነገረው ትንቢት፣ የሚጠበቀው ሱባኤ እንደደረሰ የሚያበስር በመሆኑ ጾመ አዳም ይባላል፡፡ አዳም ቢበድልም ንስሐ ገብቶ በማልቀሱ ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድንሀለሁ ብሎ የተነገረው ተስፋ መድረሱን፣ ምሥጢረ ሥጋዌ እውን ሊሆን መቃረቡን የሚያስረዳ ጾም ነው፡፡
ነቢያትም የምሥጢረ ሥጋዌ ነገር ተገለጦ ስለታያቸው፣ ክርስቶስ ለሰው ልጅ የሚከፍለውን የፍቅር ዋጋ በትንቢት ተመልክተው ጾመውታልና ጾመ ነቢያት ይባላል፡፡ ይህ ጾም የራቀውን አቅርቦ፣ የረቀቀውን አጉልቶ ስላሳያቸው እስከሞት ድረስ ቢደበደቡም፣ ከመከራው ጽንአት የተነሣ ዋሻ ለዋሻ፣ ፍርኩታ ለፍርኩታ ቢንከራተቱም፣ የፍየል ሌጦ ለብሰው ቢዞሩም የተስፋው ቃል ሁሉን አስረስቶአቸው ከትንቢቱ ባለቤት ጋር በመንፈስ ተዋሕደው አልፈዋል፡፡
ከዚህ በተጨማሪም ሐዋርያት ምን ሠርተን የክርስቶስን ልደት እንቀበለው ብለው ስለጾሙት ጾመ ሐዋርያት ተብሎ ይጠራል፡፡
ጾመ ነቢያት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም ወልደ አብን ፀንሼ ምን ሠርቼ እወልደዋለሁ በማለት ጾማዋለችና ጾመ ማርያም ይባላል፡፡ ይህን ያለችው በመደነቅ፣ አንድም በትሕትና አንድም ቀደምት አባቶቿ ነቢያት ሲጾሙት አይታ ጾማዋለች፡፡ እንዴት ፀንሼ እወልደዋለሁ ማለት ጥርጥር ሳይሆን ተደሞ፣ መደነቅ የነገረ ልደቱን አይመረመሬነት ይገልጻል፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ትሕትና ነው፡፡ እግዚአብሔር አምላክ ቅድስናዋን አይቶ በብስራተ መልአክ አማካኝነት ክርስቶስን እንደምትወልድ ቢነግራትም የትሕትና እናት ናትና ምን ሠርቼ የሰማይና ምድርን ፈጣሪ እችለዋለሁ ስትል ጾማዋለች፡፡
ይህ ጾም ጾመ ፊልጶስም ይባላል፡፡ ሐዋርያው ፊልጶስ በአረማውያን ዘንድ ገብቶ ሲያስተምር በሰማዕትነት ሲሞት አስከሬኑ ከደቀመዛሙርቱ ስለተሰወረ እግዚአብሔር የተሰወረውን የመምህራቸውን አስከሬን እንዲገልጽላቸው ከኅዳር አስራ ስድስት ጀምረው ሲጾሙ በሦስተኛው ቀን የመምህራቸው አስከሬን ቢመልስላቸውም ጾሙን ግን እስከ ልደት ቀጥለዋል፡፡  ጾምን ትእዛዝ ስለሆነ ብቻ ሳይሆን የፍቅርና የበረከት ምንጭ በመሆኑ ጭምር ደስ እያለን ብንጾመው የቅዱሳኑ በረከት ያድርብናል፡፡

ጾሙን ጾመ ሥርየት ፤ ጾመ መድኃኒት ያድርግልን ፤
ለብርሃነ ልደቱ በሰላም እና በጤና ያድርሰን ፤
ጾመን ለማበርከት ያብቃን - አሜን ፡፡

አባ ሳሙኤል ዘዋልድባ



    በአብ ስም አምኜ አብን ወላዲ ብዬ፣ በወልድ ስም አምኜ ወልድን ተወላዲ ብዬ በመንፈስ ቅዱስ ስም አምኜ መንፈስ ቅዱስን ሰራጺ ብዬ በማመን ምንም እንኳን በስም በአካል በግብር ሦስት ቢሆኑም በመለኮት ዓለምን በመፍጠርና በማሳለፍ በህልውና በመፍረድ አንድ አምላክ ብዬ በማመንና በሥላሴ አንድነትና ሦስትነት በመታመን ስለ አባ ሳሙኤል ዘዋልድባ ከብዙ በጥቂቱ ለመጻፍ እንዲህ እንጀምራለን።
“…. ከመ እግነይ ለስምከ እግዚኦ ኪያየ ይጸንሑ ጻድቃን እስከ ሶበ ተዐስየኒ።” (“ዋጋዬን እስክትሰጠኝ ድረስ ጻድቃን እኔን ይጠብቃሉ።”) መዝ.፻፵፩፡፯ (141፡7)
†አባ ሳሙኤል ዘዋልድባ†
ትውልዳቸው ከዘርዐ ጌዴዎን ገበዘ አክሱም ነው። አ
ባታቸው እስጢፋኖስ እናታቸው አመተማርያም ይባላሉ። ለመምህር ሰጥቷቸው ሲማሩ አድገው ኋላ ወላጆቻቸው በሞት ሲለዩአቸው ደብረበን ኮል ስገብተው ስርዓተ ምንኩስናን ከአበው እያጠኑ ለትልቁም ለትንሸሹም በትህትና እየታዘዙ ውሃ እየቀዱ እንጨት እየሰበሩ በትኀርምትና በጸለሎት ይኖሩ ነበር። ሰይጣን በውዳሴ ከንቱ ጾር ቢመጣባቸው ከማኀበረ መነኮሳቱ ተለይተው በተባሕትዎ ለመኖር ሽተው ወጥተው ሲሄዱ ተከዜ ደረሱ። ወንዙ ሞልቶ የማያሻግራቸው ቢሆን ውሃውን በትምህርተ መስቀል ባርከው በአንድ እጃቸው መጽሐፍ በአንድ እጃቸው መብራት እንደያዙ ገብተው መብራቱ ሳይጠፋ መጽሐፉም ሳይበላሽ ተሻግረዋል። ዋልዲባ ሲደርሱ ጌታ እዚህ ተቀመጥ ስላላቸው ገዳም ገድመው ሥርዓተ ምንኩስናን እያስተማሩ ተቀመጡ። ዛሬ በዋልድባ የሚያመሰግኑበት ውዳሴ ማርያም ቅዳሴ ማርያምን ከተከዜ ወዲህ ያመጡ እሳቸው ናቸው። ይህን እየጸለዩ ሲሄዱ ክንድ ከስንዝር መሬት ለቀው ይታቱ ነበር። አንድ ቀንም ይህንን ጸሎት ደግመው ውኃውን ሲባርኩት ኀብስተ ሕይወት ሆነላቸው። ከነ ደቀመዛሙርቶቻቸው ተመግበውታል። እመቤታችን የፍቅር መግለጫ ነጭ ዕጣንና ዕንቁ ሰጥታቸዋለች። ውዳሴዬን ከቅዳሴዬ አንድ አድርጎ የደገመውን አንተ ከገባህበት መካነ ሕይወት (የሕይወት ቦታ) አስገበዋለሁ ብላ ተስፋ ሰጥታቸዋለች። ጊዜ ዕረፍታቸው ሲደርስ ጌታ በስብሐተ መላዕክት ተገልጾ በስምህ የተማጸነውን በጎ የሰራውን ዜና ገድልህን የጻፈ፣ ያጻፈ፣ የያነበበ፣ የተማረ፣ የያስተማረውን፣ እስከ ዐሥር ትውልድ ድረስ ምሬልሃለሁ። በዚህ ቦታ የሚሰበሰቡ ልጆችህን ከእዳ ከፍዳ እሰውርልሃለሁ። አላቸው። እንኪያስ ቦታዋን ባርክልኝ ብለው እንደ መሶብ አንስተው አስባርከዋት በገዳመ ዋሊ ታኀሳስ ፲፪ (12) ቀን ዐርፈዋል። የአባታችን ረድኤትና በረከታቸው በሁላችን ላይ ለዘላለሙ ጸንቶ ይኑር አሜን።
“በቀረውስ፥ ወንድሞቼ ሆይ፥ በጌታ ደስ ይበላችሁ። ስለ አንድ ነገር መልሼ ልጽፍላችሁ እኔን አይታክተኝም ለእናንተ ግን ደኅና ነው። ከውሾች ተጠበቁ፥ ከክፉዎችም ሠራተኞች ተጠበቁ፥ ከሐሰተኛም መገረዝ ተጠበቁ። እኛ በመንፈስ እግዚአብሔርን የምናመልክ በክርስቶስ ኢየሱስም የምንመካ በሥጋም የማንታመን እኛ የተገረዝን ነንና።“ ፊሊ.፫፡፩¬-፫ (ፊሊ.3፡1¬-3
ምንጭ፡¬- በማኀበረ ቅዱሳን ትምህርት ክፍል የተዘጋጀ ነገረ ቅዱሳን ቁጥር ሁለት መጽሐፍና የኢትዮጵያውያን ቅዱሳን ታሪክ በሊቀ ብርሃናት መርቆሬዎስ አረጋ የተዘጋጀ።
ካለመኖር ወደ መኖር ያመጣኝ፣ ካለማወቅ ወደ መረዳት ያደረሰኝ አነሳስቶ ላስጀመረኝ አስጀምሮ ላስፈጸመኝ ጥንት ላሌለው ቀዳማዊ ፍጻሜ ላሌለው ድህራዊ ያልኖረበት ጊዜ የሌለ የማይኖርበት ጊዜም የማይኖር የዘላለም ንጉስ ሁሉን ቻይ ፈጣሪ እግዚአብሔርን በራስ ፀጉሬ ቁትር በአጥንቶቼም ልክ አመሰግናለሁ፡፡ እድሜ ለንሰሐ ዘመን ለፍሰሃ ሰጥቶኝ ይህችን ታህል ስለ አባታችን እንድመሰክር የረደኝ አምላክ ስሙ የተመሰገነ ይሁን።
አመስግኛት የማልሰለች፣ ስለሷ ተናግሬ የማይደክመኝ፣ በሰማይ ያሉ መላእክት በምድርም የሚኖሩ የአዳም ዘር ሁሉ የሚያመሰግኗት በአማላጅነቷ ሁል ጊዜ የማትለየኝ ከፀሐይ ሰባት እጅ የምታበራ የብርሃን እናት የሁሉ እመቤት የአምላክ እናት ከተመረጡ የተመረጠች ከተለዩ የተለየች ከተከበሩ የተከበረች እናቴ እመቤቴ ድንግል ማርያም በቃላት ልገልጸው ከምችለው በላይ አመሰግናለሁ፡፡

የእግዚአብሔር፣ቸርነት የድንግል ማርያም አማላጅነት፣ የቅዱሳን መላእክት ተራዳኢነት፣ የጻድቃን፣ የሰማዕታት፣ የቅዱሳን ሐዋርያት፣ የቅዱሳን አበው መነኮሳት፣ የቅዱሳት አንስት፣ የደናግላንና የቅዱሳን ሁሉ ምልጃና ቃል-ኪዳናቸው ባለንበት ከሁላችን ጋር ይሁን ይቆየን፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር ለዘበቅዱሳኒሁ ይሴባሕ ይእዜኒ ወዘልፈኒ ወለዓለም ዓለም አሜን፡፡ ወአሜን ለይኩን ለይኩን፡፡ አነሳስቶ ያስጀመረኝ አስጀምሮ ያስጨረሰኝ የቅዱሳን አባቶቻችን አምላክ ይክበር ይመስገን አሜን፡፡

ነገረ ማርያም በብሉይ ኪዳን

                                                          ምዕራፍ አንድ
                               ነገረ ማርያም ከኦሪት ዘፍጥረት እስከ ኦሪት ዘዳግም
                                                          ክፍል አንድ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን    
ታቦት ዘዶር: የአምላክ ታቦት (ማደሪያ) የሆነች ቅድስት ድንግል ማርያም በኢየሩሳሌም ሰማያዊት በምትገኘው ታቦት ትመሰላለች::እግዚአብሄር አምላክ በዚህች በእለተ እሁድ ከፈጠራቸው ከሰባቱ ሰማየት አንዷ በመንበረ መንግስት አንፃር ያለችው ኢየሩሳሌም ሰማያዊት ትገኛለች (ገላትያስ 4*26 : ዕብራውያን 12*12)ይህቺውም ሰማይ እንደ ቤተመቅደስ አራት ማእዘን ያላት ስትሆን አስራ ሁለት ደጃፎች አሏት !! በዚያም የብርሃን አዕማድ ደግፎ የብርሃን ክዳን ከፍክፎ ዙሪያዋን በክዋክብት አምሳል የብርሃን መርገፍ አዙሮባታል::
     ዮሃንስ ወንጌላዊው ስለ ኢየሩሳሌም ሰማያዊት ነገር በራእዩ ላይ <<የእግዚአብሄር ክብር ያለባትን ቅድስቲቱን ከተማ ኢየሩሳሌምን ከሰማይ ከእግዚአብሄር ዘንድ ስትወርድ አሳየኝ ብርሃንዋም እጅግ እንደከበረ ድንጋይ እንደ ኢያስጲድ ድንጋይ ሆኖ እንደ ብርሌ የጠራ ነበር ታላቅና ራዥም ቅጥር ነበራት አስራ ሁለት ደጆች ነበሯት >> (ራእይ 21*11-12)በማለት ተናግሮላታል::
     በዚህች በሰማያዊቲየርሳሌም ጌታ ወርዷ ቁመቷ የትስተካከለ የብርሃን ፅላት ቀርፆ በውስጧ አኑራል( ራእይ11*19):: ይህቺውም ታቦት ዘዶር ተብላ ትጠራለች ሊቁ ኤጲፋኒዮስ የሥነ ፍጥረትን ነገር በሚናገረው መጽሀፍ << ወውስቴታ ታቦት ዘዶር ዘያበርህ በጸዳለ ሥሉስ ቅዱስ >> (በስላሴ ጸዳልየሚያበራ ታቦት ዘዶር በውስጧ በኢየሩሳሌም ሰማያዊት አለ በማለት የተናገረላት ይህች በኢየሩሳሌም ሰማያዊት ያለችው ታቦት ዘዶር የአማናዊት ታቦት የሥላሴ ማደሪያ የሆነችው በምድረ ኢየሩሳሌም የተገኘችው የቅድስት ድንግል ማርያም ምሳሌ ናት::
     ይኸውም መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ከእግዚአብሄር ዘንድ ትልኮ ቅድስት ድንግል ማርያምን የአምላክ ታቦት (ማደሪያ) መሆኗን <<መንፈስ ቅዱስ በአንቺ ላይ ይመጣል የልዑል ኅይል ይጸልልሻል ስለዚህ ደግሞ ከአንቺ የሚወለደው ቅዱስ የእግዚአብሄር ልጅ ይባላል >> (ሉቃስ 1*35) በማለት አጉልቶ መስክሮላታል:: ይህንን ምስጢር በጥልቀት የተረዳ አባ ሕርያቆስም በቅዳሴ ማርያም መጽሀፉ << ወውስቴታ ታቦት ዘዶር እንተ ይእቲ እግዝትነ ማርያም>> (ከእነርሱም ጋራ ታብይ ዘዶር ወዳለችበት ያግባችሁ ይህቺውም እመቤታችን ማርያም ናት :; በማለት ታቦት ዘዶር የእውነተኛይቱ የአምላክ ታቦት የድንግልማርያም ምሳሌ መሆናን አጉልቶ ገልጾታል::
ይቆየን
የቅድስት ድንግል ድንግል ማርያም አማላጅነት
 የሰባቱ ሊቃነ መላእክት የቅዱሳን የሰማእታት የቅዱሳን አባቶች ተራዳኢነት አይለየን 
ወስብሐት ለእግዚአብሔር ለዘበቅዱሳኒሁ ይሴባሕ ይእዜኒ ወዘልፈኒ ወለዓለም ዓለም አሜን፡፡ ወአሜን ለይኩን ለይኩን፡፡

መጋቤ ሐዲስ ሮዳስ 2002ዓ/ም

Monday, November 19, 2012

ሊቀ መልዐክ ቅዱስ ሚካኤል



በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ
እንኳን ለመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ዓመታዊ ታላቅ ክብረ በዓል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን !!!!!
ድርሳን ዘቅዱስ ሚካኤል
(እም ቅዱስ መጽሐፍ)

ቅዱስ ማለት ልዩ፥ ክቡር ማለት ነው፤ ሚካኤል ማለት ደግሞ «መኑ ከመ አምላክ፥ እንደ እግዚአብሔር ያለ ማነው?» ማለት ነው። ሚካኤል የሚለው ስም ቃሉ የዕብራይስጥ ነው፤ ሚ - የሚለው «መኑ» ማለት ነው፥ ካ - የሚለው «ከመ» ማለት ሲሆን፥ ኤል - ማለት ደግሞ «አምላክ» ማለት ነው። ይህን ማለትም የቅዱስ ሚካኤልን ስም በጠራን ቊጥር የምንመሰክረው ስለ እግዚአብሔር ነው፤ በመሆኑም እግዚአብሔርን በባሕርይ የሚመስለው፥ በሥልጣንም የሚተካከለው፥ በምድርም በሰማይም እንደሌለ የሚናገር ልዩ፥ ክቡር ስም ነው። የነቢያት አለቃ ሙሴ ባሕረ ኤርትራን ለሁለት ከፍሎ ሕዝቡን
ያሻገረለትንና ፈርዖንን ከነሠራዊቱ ያሰጠመለትን አምላክ እግዚአብሔርን በመዝሙር ሲያመሰግን፥ «አቤቱ በአማልክት መካከል (በስም አማልክት ከሚባሉ፥ በስመ አማልክት ከሚጠሩ፥ አንድም አማልክት ዘበጸጋ ከተባሉ ከነቢያት ከካህናት መካከል) አንተን የሚመስል ማነው? በቅዱሳንም ዘንድ እንደ አንተ የከበረ ማነው?» ብሏል። ዘጸ ፲፭፥፲፩። ቅዱስ ዳዊትም፦ «አቤቱ፥ ከአማልክት የሚመስልህ የለም፤» ብሏል። መዝ ፹፭፥፰።
፩፥፩፦ «ስሜ ድንቅ ነውና ለምን ትጠይቃለህ?» መሳ ፲፫፥፲፯
የእስራኤል ልጆች በእግዚአብሔር ፊት ክፉ በመሥራታቸው፥ እግዚአብሔር በፍልስጥኤማውያን እጅ ለአርባ ዓመት አሳልፎ ሰጥቷቸው ነበር.። በዚህ ዘመን ከዳን ወገን ማኑሄ የሚባል አንድ ሰው ነበረ፥ ሚስቱም መካን ስለነበረች ልጅ አልወለደችም ነበር። የእግዚአብሔር መልአክ ተገልጦ እንደምትፀንስ፥ ወንድ ልጅም እንደምትወልድ፥ ልጁም ከእናቱ ማኅፀን ጀምሮ ለእግዚአብሔር የተለየ ናዝራዊ እንደሚሆን ነገራት። የሚያሰክር መጠጥ እንዳትጠጣ፥ የረከሰም ነገር እንዳትበላ፥ በልጁም ራስ ላይ ምላጭ እንዳይደርስ (ፀጉሩን እንዳትላጨው) አስጠነቀቃት። እርሷም ተመልሳ የሆነውን ሁሉ ለባሏ ነገረችው፤ «የእግዚአብሔር ሰው ወደ እኔ መጣ፥ መልኩም እንደ እግዚአብሔር መልአክ እጅግ የሚያስደነግጥ ነበረ፤ ከወዴትም እንደመጣ ጠየቅሁት፥ እርሱም ስሙን አልነገረኝም፤» አለችው።
ማኑሄም፥ «ጌታ ሆይ፥ ወደ እኛ የላክኸው የእግዚአብሔር ሰው እባክህ እንደገና ወደ እኛ ይምጣ፤ ለሚወለደውም ልጅ ምን እንደምናደርግ ያስገንዝበን፤» ብሎ ወደ እግዚአብሔር ለመነ። እግዚአብሔርም የማኑሄን ቃል ሰማ፤ የእግዚአብሔርም መልአክ በእርሻ ውስጥ ሳለች እንደገና ወደ ሴቲቱ መጣ፥ እርሷም ፈጥና ባሏን ጠራችው፥ «እነሆ፥ አስቀድሞ ወደ እኔ የመጣው ያ ሰው ደግሞ ተገለጠልኝ፤» ብላ ነገረችው። እርሱም፦ «ከሚስቴ ጋር የተነጋገርህ አንተ ነህን?» ብሎ ቢጠይቀው «እኔ ነኝ፤» ሲል መለሰለት። ማኑሄም፦ «እነሆ ቃልህ በደረሰ ጊዜ የልጁ ነገር፥ ግብሩስ ምንድነው?» ብሎ ዳግመኛ ጠየቀ። መልአኩም ለሴቲቱ ነግሯት የነበረውን ሁሉ መልሶ ነገረው። ማኑሄ ለመልአኩ የፍየል ጠቦት ለማዘጋጀት ቢፈልግም፦ «አንተ የግድ ብትለኝ እህልህን አልበላም፥ የሚቃጠለውንም መሥዋዕት ብታደርግ ለእግዚአብሔር አቅርብ፤» አለው። ምክንያቱም ቅዱሳን መላእክት ቅድሚያ የሚሰጡት ለእግዚአብሔር ክብር ነው። እነርሱን ግን እግዚአብሔር ራሱ እንደሚያከብራቸው እንደሚያስከብራቸውም ያውቃሉ።
ማኑሄ የተገለጠላቸው የእግዚአብሔር መልአክ እንደሆነ አላወቀም፥ ሚስቱም አላወቀችም። በመሆኑም፦ «ነገርህ በደረሰ ጊዜ እንድናከብርህ ስምህ ማን ነው?» በማለት ጠየቀው። የእግዚአብሔርም መልአክ፥ «ስሜ ድንቅ ነው፥ ለምን ትጠይቃለህ?» ብሎታል። ማኑሄም የፍየሉን ጠቦትና የእህሉን ቊርባን በድንጋይ ላይ ለእግዚአብሔር አቀረበ። መልአኩም ተአምራት አደረገ፥ ማኑሄና ሚስቱም ይመለከቱ ነበር። ነበልባሉም ከመሠዊያው ላይ ወደ ሰማይ በወጣ ጊዜ የእግዚአብሔር መልአክ በመሠዊያው ነበልባል ውስጥ ወደ ሰማይ ዐረገ፥ ማኑሄና ሚስቱም ተመለከቱ፥ በምድርም በግንባራቸው ወደቁ። (ሰገዱለት)። ይህ መልካም የምሥራችን የተናገረ፥ የተለያዩ ተአምራትን ያደረገ፥ መሥዋዕታቸውንም ወደ ሰማይ ያሳረገ፥ የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ነው። ሚካኤል ማለት በሁለተኛ ትርጉሙ «የእግዚአብሔር ነገሩ ዕፁብ ድንቅ ነው፤» ማለት ነውና። መሳ ፲፫፥፩-፳። በዚህም የስሙ ትርጓሜ ነገረ እግዚአብሔር መሆኑን እንረዳለን።
፩፥፪፦ የእግዚአብሔር ሠራዊት አለቃ፤ ኢያ ፭፥፲፬
ከነቢያት አለቃ ከሙሴ በኋላ በእርሱ እግር ተተክቶ የእግዚአብሔርን ሕዝብ የመራው ኢያሱ ነው። የመረጠውም ሰው ሳይሆን እግዚአብሔር ነው። እግዚአብሔርም፦ «በሕይወትህ ዘመን ሁሉ የሚቋቋምህ የለም፤ ከሙሴ ጋር እንደነበርሁ እንዲሁ ከአንተ ጋር እሆናለሁ፥ አልጥልህም፥ ቸልም አልልህም፤» ብሎታል። ኢያ ፩፥፭። ይህ እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር የሆነለት ታላቅ ሰው ኢያሱ የቅዱሳን መላእክት ተራዳኢነት አስፈልጐታል። ምክንያቱም እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር ለመሆኑ ምልክቱ ቅዱሳን መላእክት ናቸውና። እግዚአብሔር ባለበት ቅዱሳን መላእክት አሉ፥ ቅዱሳን መላእክትም ባሉበት እግዚአብሔር አለ። ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በተወለደባት ሌሊት የምሥራቹን «እነሆ፥ ለእናንተና ለሕዝቡ ሁሉ ደሰታ የሚሆን ታላቅ የምሥራች እነግራችኋለሁና አትፍሩ፤ እነሆ፥ ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኃኒት ተወልዶላችኋል፤ ይኸውም ቡሩክ ጌታ ክርስቶስ ነው።» በማለት ለእረኞች የነገሯቸው ቅዱሳን መላእክት ናቸው። እረኞቹም፦ «እስከ ቤተልሔም እንሂድ፥ እግዚአብሔርም የገለጠልንን ይህን ነገር እንወቅ፥ አሉ።» ሉቃ ፪፥፮-፲፭። በዚህም ቅዱሳን መላእክት የገለጡላቸውን ምሥጢር እግዚአብሔር ገለጠልን ብለዋል።
ኢያሱ ወልደ ነዌ፥ ሕዝቡን እየመራ በኢያሪኮ አጠገብ ሳለ ዐይኑን አንሥቶ ቢመለከት እነሆም የተመዘዘ ሰይፍ በእጁ የያዘ ሰው በፊቱ ቆሞ አየ። ወደ እርሱም ቀርቦ «ከእኛ ወገን ወይስ ከጠላቶቻችን ወገን ነህን?» አለው። እርሱም «እኔ የእግዚአብሔር ሠራዊት አለቃ ነኝ፤ አሁንም ወደ አንተ መጥቻለሁ፤» ብሎታል። ኢያ ፭፥፲፫-፲፭። የእግዚአብሔር ሠራዊት የሚባሉት ቅዱሳን መላእክት ናቸው። «ያዕቆብም መንገዱን ሄደ፥ በዓይኖቹም የእግዚአብሔርን ሠራዊት ከትመው አየ፥ የእግዚአብሔር መላእክትም ተገናኙት። ያዕቆብም ባያቸው ጊዜ እነዚህ የእግዚአብሔር ሠራዊት ናቸው አለ፤» ይላል። ዘፍ ፴፪፥፩-፪። ቅዱስ ዳዊትም፦ «ሠራዊቱ ሁሉ፥ ፈቃዱን የሚያደርጉ አገልጋዮቹ፥ እግዚአብሔርን ያመሰግኑታል፤» ብሏል። መዝ ፩፻፪፥፳፩። የእነዚህም (የእግዚአብሔር ሠራዊት) አለቃቸው ቅዱስ ሚካኤል ነው። ይኽንንም ሐዋርያው ቅዱስ ይሁዳ «የመላእክት አለቃ ሚካኤል» በማለት መስክሮለታል። ይሁዳ ፩፥፲፪።
፩፥፫፦ ሚካኤልና መላእክቱ ዘንዶውን ተዋጉት፤ ራእ ፲፪፥፯
ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ በደሴተ ፍጥሞ በግዞት ሳለ በተመለከተው ራእይ ሃላፊያትና መጻእያት ተገልጠውለት ስለነበረ፥ «በሰማይም ሰልፍ (ጦርነት) ሆነ፤» ካለ በኋላ «ሚካኤልና መላእክቱም ዘንዶውን ተዋጉት፥ ዘንዶውም ከነሠራዊቱ ተዋጋቸው። አልቻላቸውምም፥ ከዚያም በኋላ በሰማይ ቦታ አልተገኘላቸውም። ዓለሙን ሁሉ የሚያስተው ዲያቢሎስና ሰይጣን የሚባለው ታላቁ ዘንዶ እርሱም የቀደመው እባብ ተጣለ፥ ወደ ምድርም ተጣለ፥ መላእክቱም (የዘንዶው ሠራዊት) ከእርሱ ጋር ተጣሉ፤» ብሏል። ራእ ፲፪፥፯-፱።
ታሪክ፦ ሰይጣን በክህደቱ አጥቶት እንጂ ክብርም ፥ ኃይልም፥ ሥልጣንም ነበረው። በአሥሩ የመላእክት ከተሞች በተሾሙ አሥር የመላእክት አለቆች ላይ የአለቃ አለቃ ነበረ። የተፈጠረው የመላእክት አለቃ ሆኖ ነው። ይኽንንም ቀሌምንጦስ ተናግሮታል። እግዚአብሔር መላእክትን በነገድ መቶ ፥ በከተማ አሥር አድርጐ ፈጥሮ ተሰወራቸው። ይህም ካልፈለጉኝ አልገኝም ፥ ባሕርዬም አይመረመርም ሲላቸው ነው። ወዲያው፦ «እኛ ምንድር ነን? ከየት መጣን ? ማንስ ፈጠረን? በራስ በራሳችን ተፈጠርን ? ወይስ ከሌላ ነው?» አሉ። ሳጥናኤል ከበታቹ እንዲህ ሲሉ ሰማ። ከበላዩ ደግሞ «ፈጠርኳችሁ፤» የሚል አጣ። በቦታው ከሁሉ በላይ አድርጎ ፈጥሮት ነበርና «እኔ ፈጠርሁ፤» ብሎ አሰበ ፥ አስቦም አልቀረ «እኔ ፈጠርኋችሁ፤» አለ። ይኽን ሰምተው «ሰጊድ ይገባዋል፤» ያሉ አሉ። «እኛም እንደ እርሱ ነን፤» ያሉም አሉ። « አምላክ ነኝ ያለስ ከእርሱ በቀር ሌላ የለምና ፥ ይሆንን?» ብለው የተጠራጠሩ አሉ። ሀልዎተ እግዚአብሔርን ሳይመረምሩ የቀሩም አሉ። እኲሌቶቹ ግን ፦ «በምን ፈጠርኋችሁ ይለናል፥ በቦታ ከበላይ በመሆን ፈጠርኋችሁ እንዳይለን ፥ እኛ የበታቾቻችንን መቼ ፈጠርናቸውና ነው?። በዚያውስ ላይ ምቀኞቹ አይደለንም፤ በእውነት ፈጣሪ ከሆነ ፈጥሮ ያሳየን ።» ብለው፦ «ፈጥረህ አሳየን፤» አሉት። እርሱም እፈጥራለሁ ብሎ ፥ እጁን ወደ እሳት ቢጨምር ፈጀውና « ዋይ» አለ። በዚህን ጊዜ «በአፍአ ያለውን (የሚነገረውንና እና የሚሠራውን ብቻ የሚያውቅ) አምላክ ቢሆን ነው እንጂ ውሳጣዊውን (ልብ ያሰበውን የሚያውቅ) አምላክ ቢሆን ኖሮ ገና ሳስበው ለምን አሰብከው ፥ ባለኝ ነበር ፤» አለ። ወዲያው ልቡን ተሰማውና «ዋይ» አለ። እግዚአብሔር ግን ፈወሰው። ይህንንም ማድረጉ ንስሐ ቢገባ እንደሚምረው ሲነግረው ነበር።
ከዚህ በኋላ በመላእክት ሽብር ቢጸናባቸው፦ መልአከ ሰላም ቅዱስ ገብርኤል፦ «ንቁም በበህላዌነ እስከ ንረክቦ ለአምላክነ ፤ አምላካችንን እስክናገኘው ድረስ በየህልውናችን ጸንተን እንቁም ፤» በማለት አጽንቷቸዋል። ይህም በጎ አርበኛ ጦር በተፈታ ጊዜ «አይዞህ ባለህበት ጽና፤» ብሎ እንደሚያጸናው ማለት ነው።« ወበእንተዝ ደለዎ ይፁር ዜናሃ ለማርያም ፤ በዚህ ምክንያት የድንግል ማርያምን ዜና ያደርስ ፥ ብሥራቷን ይናገር ዘንድ ተገባው ፤ » እንዲል ፥ ብሥራት ተሰጥቶታል። «በስድስተኛው ወር (አምስት ሺህ አምስት መቶ ዘመን ሲፈጸም ፥ ስድስተኛው ሺህ ደግሞ ሲጀምር) መልአኩ ገብርኤል . . . ወደ አንዲት ድንግል ተላከ» ይላል። ሉቃ ፩፥፳፮።
እግዚአብሔርም ጨርሶ ሳያስታቸው ብሎ እርሱ (ሳጥናኤል) በሌለበት በኲል በምሥራቅ ባሕረ ብርሃንን አፍስሶላቸዋል። ከዚህም ጋር ስሙ የተጻፈበት መጽሔተ ብርሃን ቢሰጣቸው አንድነቱ ሦስትነቱ(ምሥጢረ ሥላሴ) ተገልጦላቸው « አሐዱ አብ ቅዱስ ፥ አሐዱ ወልድ ቅዱስ ፥ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ፤» ብለው አመስግነውታል። እርሱን ግን ባደረው ጨለማ ጠቅልሎ በዕለተ እሑድ ከኢየሩሳሌም ሰማያዊት ወደ ኢዮር አውርዶታል። ከሰባቱ ሰማያት ሦስቱ ፦ ኢዮር ፥ራማ፥ ኤረር የመላእክት ናቸው። በውስጣቸውም አስር የመላእክት ከተሞች አሉ። በእነርሱም ላይ አስር አለቆች ተሹመዋል። እግዚአብሔር ሳጥናኤል በሌለበት በኲል ባሕረ ብርሃንን ያፈሰሰላቸው «እኔ ፈጠርኩ » እንዳይል ነው።
ሳጥናኤል በኢዮር ሆኖ በዕለተ ሠሉስ የተፈጠሩ ዕፅዋት፥ አዝርዕት ፥ አትክልት ፥ጽጌያትን አይቶ እንዳያደንቅ፦ «እንዲህ አድርጐ አከናውኖ የፈጠረለት ቢኖር ነው፥ » አለ። እግዚአብሐርም «ከወደድሃት በዚያ ላኑርህ ፤» ቢለው «ደገኛይቱን ማን ከልክሎኝ ፤» አለ። ከዚህ በኋላ ለሚካኤልና ለገብርኤል «እናንተ ኢየሩሳሌም ሰማያት ይሏችኋል ፥ ሰባቱ ሰማያት እንኳ አያህሏትም። እኛ ከጩኸት በቀር የተጠቀምነው የለም። ገዢ ነኝ የሚለውን ወግተን እጅ እናድርግ።» ብሎ ላከባቸው። እነርሱም የተላኩትን ከንጉሥ ከተማ እንደገባ ዕብድ ውሻ አድርገው ሰደዷቸው። ተመልሰውም አልተቀበሉንም ቢሉት ፦ «ቀለምጺጸ እሳት (የእሳት ፍንጣሪ) የሆኑ ሚካኤል ገብርኤል በእኔ ዘንድ ምን ቁም ነገር ናቸው። ይልቁንስ ኑ ተሸከሙኝና እንሂድ ፤» አላቸው። በዚህን ጊዜ በአርባዕቱ እንስሳ (በኪሩቤል) አምሳል አራት ሁነው ተሸክመውት ሽቅብ እወጣለሁ ቢል ኃይል ተነሥቶታል። ወደ ታች እንጂ ወደ ላይ መውጣት የማይቻለው በመሆኑም ፦ «ጐየ እግዚእ ምስለ አርያሙ፤ እግዚአብሔር ሰማዩን (ጽርሐ አርያምን) ጠቅልሎ ሸሸ፤» ብሎ ተመለሰ።
ቅዱሳን መላእክት ግን ፍጥረትን ሲፈጥር እያዩ ያመሰግኑ ነበር። በዕለተ ረቡዕ ፀሐይ ፥ ከዋክብት ፥ ጨረቃ ፥ ሲፈጠሩ አይተው አመስግነው አመስግን ቢሉት ፦ «አንሰ ዕድው (ውፁዕ) እምዝንቱ ኅሊና፤» እንዲል፦ «እኔ ከዚህ ውጪ ነኝ ፥ ባይሆን አራተኛ አድርጋችሁ ብታመሰግኑኝ እወዳለሁ፤» አላቸው። እነርሱም «ይህ ስሑት ፍጥረት እንዲህ እያለ እስከ መቼ ሲታበይ ይኖራል?» ብለው ሄደው ቢገጥሙት ድል አደረጋቸው። ሁለተኛም ቢገጥሙት ዳግመኛ ድል አደረጋቸው። በዚህን ጊዜ፦ «እኛስ ለአምላክነትህ ቀንተን ነበረ ፥ አንተ ግን ፈቃድህ ሳይሆን ቀረ፤» ብለው ወደ እግዚአብሔር ቢያመለክቱ ፦ «ፈቃዳችሁ ፈቃዴ ነው ፥ ነገር ግን ድል የሚነሣበትን (የሚሸነፍበትን) ታውቁ ዘንድ ነው፤» ብሎ ስሙ የተጻፈበትን ትእምርተ መስቀል ሰጣቸው። ያን ይዘው በዕለተ ረቡዕ ወደዚህ ዓለም አውርደውታል። በዚህን ጊዜ የእርሱ ወገኖች ለሦስት ተከፍለዋል። ሀለዎተ እግዚአብሔርን ሳይመረምሩ የቀሩ በአየር ቀርተዋል። ይሆን ፥ አይሆን ብለው የተጠራጠሩ በዚህ ዓለም ቀርተዋል። « አምላክ ነው ፥ ሰጊድ ይገባዋል፤» ያሉ አብረው እንጦሮጦስ ወርደዋል።
፩፥፬፦ ታላቁ አለቃ ሚካኤል ይነሣል፤ ዳን ፲፪፥፩
ቅዱስ ሚካኤል ለእግዚአብሔር መንጋ እረኛቸው ነው። ነቢየ እግዚአብሔር ዳዊት፦ በመዝ ፴፫፥፯ ላይ «የእግዚአብሔር መልአክ በሚፈሩት (ፈሪሃ እግዚአብሔር ባላቸው) ሰዎች ዙሪያ ይሰፍራል፥ (ይከትማል፥ የእሳት አጥር ይሆናል)፥ ያድናቸውማል፤» እንዳለ፥ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል በተለይም በፍጻሜ ዘመን ከሚመጣው መከራ የእግዚአብሔርን ሕዝብ ያድናል። ይህ ምሥጢር የተገለጠለት ነቢየ እግዚአብሔር ዳንኤል፦ «በዚያም ዘመን ስለ ሕዝብህ ልጆች የሚቆመው (በአማላጅነት በተራዳኢነት የሚቆመው) ታላቁ አለቃ ሚካኤል ይነሣል፥ ሕዝብም በምድር ከተፈጠረ ጀምሮ እስከዚያ ዘመን ድረስ እንደ እርሱ ያለ ያልሆነ የመከራ ዘመን ይሆናል፤» ብሏል። ዳን ፲፪፥፩። በዚህም፦ ገናና መልአክ፥ የመላእክት አለቃ፥ አማላጅና ተራዳኢ መሆኑን መስክሮለታል። ስለዚያች ቀን፥ ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ፥ «ያንጊዜ ዓለም ከተፈጠረ ጀምሮ እስከዛሬ ያልተደረገ፥ ከእንግዲህም ወዲያ የማይደረግ ታላቅ መከራ ይሆናል፤» ካለ በኋላ፥ «መላእክቱንም ከታላቅ የመለከት ድምፅ ጋር ይልካቸዋል፥ የተመረጡትንም ከሰማይ ዳርቻ እስከ ዳርቻው ከአራቱ መዐዝን ይሰበስቧቸዋል።» ብሏል። ማቴ ፳፬፥፳፩-፴፩። ቅዱስ ዮሐንስም ስለ ሓሳዊ መሲሕ ዘመን ተገልጦለት፥ «ከዚህ በኋላ ሌላ አውሬ ከምድር ሲወጣ አየሁ፤ . . . ለአውሬውም (ለፊተኛው አውሬ) ምስል ያልሰገደውን ሁሉ እንዲገደሉ ያደርጋቸዋል፤» ብሏል። ራእ ፲፫፥፲፩፣ ፲፭። እንግዲህ የዚህን ክፉ ዘመን መከራ ሥጋ ለባሽ የሆነ ሁሉ ስለማይቋቋመው የመላእክት አለቃ የቅዱስ ሚካኤልና የሠራዊቱ ተራዳኢነት አስፈልጓል። ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስም፦ «መላእክት ሁሉ መናፍስት አይደሉምን? የዘለዓለም ሕይወትን ይወርሱ ዘንድ ስለ አላቸው ሰዎችስ ይላኩ የለምን?»ያለው ለዚህ ነው። ዕብ ፩፥፲፬።
፩፥፭፦ ከዋነኞቹ አለቆች አንዱ ሚካኤል ሊረዳኝ መጣ፤ ዳን ፲፥፲፫
ነቢዩ ዳንኤል፥ በፋርስ ንጉሥ በቂሮስ በሦስተኛው ዓመተ መንግሥት በራእይ ምሥጢር ተገልጦለታል፥ ነገሩም ከእግዚአብሔር በመሆኑ ምሥጢር ነበረ፥ ታላቅ ኃይልና ማስተዋልም በራእዩ ውስጥ ተሰጥቶታል። ነቢዩ ዳንኤል ስለ ሕዝቡ ኃጢአትና ሊመጣ ስላለው መከራ ሶስት ሳምንት ሙሉ አዝኗል። (ጾም ጸሎት ይዟል)። ማለፊያ እንጀራ አልበላም፥ ሥጋና የወይን ጠጅም በአፉ አልገባም፥ ሦስቱም ሳምንት እስኪፈጸም ድረስ ራሱን ዘይት አልተቀባም። ከልጅነቱ ጀምሮ ጾም ጸሎትን አጥብቆ የያዘ ነቢይ ዳንኤል በራእይ የተገለጠለት ምሥጢረ ሥጋዌ ነው። «ዳንኤልም ከንጉሡ ማእድ እንዳይበላ፥ ከሚጠጣውም ጠጅ እንዳይጠጣ ልቡ ጨከነ፥ እንዳያበላውም የጃንደረቦቹን አለቃ ለመነው፥ እግዚአብሔርም በጃንደረቦቹ አለቃ ፊት ለዳንኤል ሞገስንና ምሕረትን ሰጠው። . . . ይህንም ነገራቸውን ሰምቶ ዐሥር ቀን ፈተናቸው። ከዐሥር ቀንም በኋላ ከንጉሡ ማዕድ ከበሉ ብላቴኖች ሁሉ ይልቅ ሰውነታቸው አምሮ ሥጋቸው ወፍሮ ታየ። አሚሳድም መብላቸውንና የሚጠጡትን ጠጅ አስቀርቶ ጥራጥሬውን ሰጣቸው፤» ይላል። ዳን ፩፥፰-፲፮።
በትንቢተ ዳንኤል ምዕራፍ ዐሥር ቊጥር ፲፫ ላይ፦ «ዳንኤል ሆይ! አትፍራ፥ ልብህ ያስተውል ዘንድ፥ ሰውነትህም በአምላክህ ፊት ይዋረድ ዘንድ ከአደረግህበት ከመጀመሪያው ቀን (ኀዘን፥ ጾም፥ ጸሎት ከጀመርክበት ዕለት) ጀምሮ ቃልህ (ጸሎትህ፥ ምልጃህ) ተሰምቷል፥ እኔም ስለ ቃልህ መጥቻለሁ። የፋርስ መንግሥት አለቃ ግን ሃያ አንድ ቀን በፊቴ ነበር። እነሆም ከዋነኞቹ አለቆች አንዱ ሚካኤል ሊረዳኝ መጣ፥ እኔም ከፋርስ ንጉሥ ጋር በዚያ ተውሁት።» የሚል እናገኛለን። ይኽንንም የተናገረው የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤል ነው። ነቢዩ ዳንኤል ጾም ጸሎት በሚይዝበት ጊዜ ዘወትር ወደ እርሱ እንደሚመጣ «ገብርኤል ሆይ! ራእዩን ለዚህ ሰው ግለጥለት፤ . . . እኔም ገና ስናገርና ስጸልይ፥ በኃጢአቴና በሕዝቤም በእስራኤል ኃጢአት ስናዘዝ፥ በአምላኬም በእግዚአብሔር ፊት ስለ ተቀደሰው ስለ አምላኬ ተራራ ይቅርታን ስጠይቅ፥ ገናም በጸሎት ስናገር አስቀድሜ በራእይ አይቼው የነበረው ሰው ገብርኤል እነሆ አየበረረ መጣ፥ በማታም መሥዋዕት ጊዜ ዳሰሰኝ።» የሚል አብነት ይገኛል። ዳን ፰፥፲፮፣ ፱፥፳።
ቅዱሳን መላእክት ሁልጊዜ ከዲያቢሎስና ከሠራዊቱ ጋር ይዋጋሉ፥ ያሸንፉማል። ቅዱስ ገብርኤል ወደ ነቢዩ ዳንኤል ሳይመጣ ለሶስት ሳምንት የዘገየበትን ምክንያት ሲነግረው «የፋርስ መንግሥት አለቃ ግን ሃያ አንድ ቀን ተቋቋመኝ፤» ብሏል። ይህም በፋርስ ንጉሥና በሠራዊቱ ካደሩ አጋንንት ጋር ሲዋጋ መሰንበቱን ያመለክታል። ይኸውም ዕለቱን ማሸነፍ ተስኖት ሳይሆን ሰይጣን ኢዮብን በከሰሰበት መንገድ እስራኤልን እየከሰሰ ቀኑን አዘግይቶበታል። ታላቁ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ፦ «ሰይጣን አዘገየኝ፤» ያለው ከዚህ ተመሳሳይ ነው። ቅዱስ ገብርኤል በሦስተኛው ሳምንት መጨረሻ ሊመጣ የቻለበትን ምክንያት ሲናገር ደግሞ «ከዋነኞቹ አለቆች አንዱ ሚካኤል ሊረዳኝ መጣ፥ እኔም ከፋርስ ንጉሥ ጋር በዚያው ተውሁት፤» ብሏል። በዚህም ቅዱሳን መላእክት እንኳ እርስ በርስ እንደሚረዳዱ እንማራለን። ይህም ድካም ተሰምቷቸው አንዳቸው የሌሎቹን እርዳታ ይፈልጋሉ ማለት ሳይሆን የአገልግሎት አንድነታቸውን የሚያጠይቅ ነው። ይህ እንዲህ ከሆነ እጅግ ደካማ የሆኑ የሰው ልጆች የኃያላን መላእክት ተራዳኢነት እንዴት አያስፈልገንም ይላሉ? በተዋሕዶ ሰው የሆነ አምላክ ኢየሱስ ክርስቶስ ለተከታዮቹ አብነት ለመሆን በጌቴሴማኔ አጸድ በጸለየበት ጊዜ «የሚያበረታታው የእግዚአብሔር መልአክም ከሰማይ ታየው፤» ይላል። ሉቃ ፳፪፥፵፫። እንግዲህ እርሱንስ ምን ሊሉት ነው?
፩፥፮፦ ከአለቃችሁ ከሚካኤል በቀር የሚረዳኝ ማንም የለም። ዳን ፲፥፳፩
ሰይጣን ሠራዊቱን አሰማርቶ በአሕዛብ ነገሥታት እያደረ የእግዚአብሔር ሕዝብ የተባሉ እስራኤልን ዘወትር በጦርነት ያስጨንቃቸው ነበር። በዚህም ምክንያት ሲወድቁ ሲነሡ፥ ሲነቀሉ ሲተከሉ፥ ሲፈርሱ ሲገነቡ፥ ሲበተኑ ሲሰበሰቡ፥ ሲሰበሩ ሲጠገኑ ኖረዋል። በዚያ ዘመን መጋቤ ብሉይ ተብሎ የሚታወቀው ቅዱስ ሚካኤል ነው። እርሱም ዘወትር ከቅዱስ ገብርኤል ጋር ሆኖ ሕዝቡን ይረዳቸው ነበር። ይኽንንም «ወደ አንተ የመጣሁት ለምን እንደሆነ ታውቃለህን? አሁንም የፋርስን አለቃ እዋጋው ዘንድ እመለሳለሁ፥ እኔም ስወጣ እነሆ የግሪኮች አለቃ ይመጣል። (ሰይጣን በግሪክ ንጉሥ አድሮ ሌላ ጦርነት ይጀምራል)። ነገር ግን በእውነት ጽሑፍ የተጻፈውን እነግርሃለሁ፥ በዚህም ነገር ከአለቃችሁ (ከመላእክት አለቃ) ከሚካኤል በቀር የሚያጸናኝ የለም።» በማለት ቅዱስ ገብርኤል ለነቢዩ ለዳንኤል ነግሮታል። ቅዱስ ገብርኤል እንዲህ ካለ እኛስ ምን እንበል?
፩፥፯፦ በመላእክት አለቃ ድምጽ፥ በእግዚአብሔርም መለከት ከሰማይ ይወርዳል፤ ፩ኛ ተሰ ፬፥፲፮
ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለጻድቃን ሊፈርድላቸው፥ በኃጥአን ሊፈርድባቸው ዳግም እንደሚመጣ ቅዱሳት መጻሕፍት በመተባበር ይመሰክራሉ። ነቢየ እግዚአብሔር ዳዊት፦ «እግዚአብሔር በግልጥ ይመጣል። አምላካችንም ዝም አይልም፥ (ይፈርዳል)፥ እሳት በፊቱ ይነድዳል፥ በዙሪያውም ብዙ አውሎ አለ።» ብሏል። መዝ ፵፱፥፫። ነቢዩ ዘካርያስም በበኲሉ የሚመጣው ከቅዱሳን ሁሉ ጋር እንደሆነ ሲናገር፦ «አምላኬ እግዚአብሔር ከቅዱሳኑ ጋር ይመጣል፤» ብሏል። ዘካ ፲፬፥፮። በአዲስ ኪዳን ደግሞ ራሱ ባለቤቱ ኢየሱስ ክርስቶስ፦ «የሰው ልጅ (ወልደ ዕጓለ እመሕያው) በጌትነቱ ቅዱሳን መላእክትን ሁሉ አስከትሎ በሚመጣበት ጊዜ፥ ያንጊዜ በጌትነቱ ዙፋን ይቀመጣል፤» ብሏል። ማቴ፳፭፥፴፩። በዕርገቱ ጊዜም ቅዱሳን መላእክት ለደቀመዛሙርቱ ተገልጠው፦ «እናንተ የገሊላ ሰዎች ሆይ፥ ወደ ሰማይ እያያችሁ ለምን ቆማችኋል? ይህ ከእናንተ ወደ ሰማይ ሲያርግ እንዳያችሁት እንዲሁ ዳግመኛ ይመጣል፤» ብለዋቸዋል። የሐዋ ፩፥፲፩። ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ስለ ትንሣኤ ሙታን ባስተማረበት ትምህርቱ፦ «ወንድሞቻችን ሆይ፥ ስለ ሞቱ ሰዎች፥ ተስፋ እንደሌላቸው ሰዎች እንዳታዝኑ ልታውቁ እንወዳለን። ኢየሱስ ክርስቶስ ሞቶ እንደተነሣ ካመንን፥ እንዲሁ እግዚአብሔር ሙታንን በኢየሱስ ያስነሣቸዋል። ይህንንም በእግዚአብሔር ቃል እንነግራችኋለን፥ ጌታችን በሚመጣ ጊዜ ሕያዋን ሆነን የምንቀር እኛ የሞቱትን አንቀድማቸውም።» ካለ በኋላ «ጌታችን ራሱ በትእዛዝ፥ በመላእክትም አለቃ ድምፅ፥ በእግዚአብሔርም መለከት ከሰማይ ይወርዳልና፤» ብሏል። ፩ኛ ተሰ ፬፥፲፫-፲፮። ይህ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ነው። እንዲህ እስከመጨረሻው ከጌታ የማይለየውን መልአክ «ለምን ስሙ ተጠራ?» ማለት ራስን ከጌታ መለየት ነው።
፩፥፰፦ የመላእክት አለቃ ሚካኤል ከሰይጣን ጋር ተከራከረ፤ ይሁ ፩፥፱
የያዕቆብ ወንድም ይሁዳ፥ ቅዱስ ሚካኤልና ሰይጣን የተከራከሩበትን ምክንያት ሲናገር፦ «የመላእክት አለቃ ሚካኤል እንኳን ስለ ሙሴ ሥጋ ከሰይጣን ጋር በተከራከረ ጊዜ የስድብን ቃል ሊናገር አልደፈረም፥ እግዚአብሔር ይገሥጽህ አለው እንጂ። እነዚህ ግን የማያውቁትን በመሳደብ ይበድላሉ፤» ብሏል። ይሁ ፩፥፱። ቅዱስ ይሁዳ፥ በዘመኑ ላሉትም ሆነ እስከ ዓለም ፍጻሜ ለሚነሡት ተሳዳቢዎች እንደተናገረው፥ የመናፍቃን ሥራቸው፥ እንደ ግብር አባታቸው እንደ ዲያቢሎስ ቅዱሳንን መርገም ነው።
የነቢያት አለቃ ሙሴ ከዚህ ዓለም በሞት የሚለይበት ጊዜ ሲደርስ፥ ከሞዓብ ሜዳ በኢያሪኮ ፊት ለፊት ወዳለው ወደ ናባው ተራራ ወደ ፈስጋ ራስ ወጣ፤ እግዚአብሔርም የከነዓንን ምድር ካሳየው በኋላ፦«ለዘርህ እሰጣታለሁ ብዬ ለአብርሃምና ለይስሐቅ ለያዕቆብም የማልሁላቸው ምድር ይህች ናት፤ እነሆም፥ በዐይንህ እንድታያት አደረግሁህ፥ ነገር ግን ወደዚያች አትገባም፤» አለው። የእግዚአብሔር አገልጋይ ሙሴም እንደ እግዚአብሔር ቃል በዚያ በሞዓብ ምድር ሞተ። በቤተ ፌጎርም አቅራቢያ በናባው ምድር ቀበሩት፥ እስከዛሬም ድረስ መቃብሩን ማንም የሚያውቅ የለም። ዘዳ ፴፬፥፩-፯። የሙሴ መቃብር እንዴት ሊታወቅ አልቻለም? የቀበረውስ ማነው?
ታሪክ፦ እግዚአብሔር የሙሴን መቃብር ከእስራኤል ሰውሮባቸዋል፥ የሰወረበትም ምክንያት ካላቸው ጽኑዕ ፍቅር የተነሣ መቃብሩን እንዳያመልኩ ነው። አንድም የተቀበረበትን ቦታ ካወቁ ጧት ማታ እየሄዱ ከመቃብሩ ላይ እያለቀሱ ኀዘን እንዳይጸናባቸው ብሎ ነው። የነቢያት አለቃ ሙሴ ወደ ተራራው ሲወጣ ሁለት መላእክት በአረጋውያን ተመስለው መቃብር ሲቆፍሩ አገኛቸው። መላእክት መሆናቸውን ግን አላወቀም። «አክብር ገጸ አረጋዊ» የሚለውን ሕግ ስለሚያውቅ «ላግዛችሁ፤» ብሎ መቃብሩን ቆፍሮ ጨረሰላቸው። እነርሱም፦ «ልክ ይዘን አልመጣንም፥ ስለዚህ ሟቹ በግምት አንተን ስለሚያክል ውስጡ ተኝተህ ለካልን፤» አሉት። እርሱም «እሺ፥በጀ፤» ብሎ ተኝቶ ሲለካ በዚያው ነፍሱ ከሥጋው ተለይታ አርፏል። ከዚህ በኋላ አፈር መልሰውበታል። የሙሴ መቃብር በሰው ዘንድ ያልታወቀው በዚህ ምክንያት ነው።
እስራኤል ዘሥጋ ከሞቱ ይልቅ የመቃብሩ መሰወር አሳዝኖአቸዋል። በዚህን ጊዜ የሰውን ችግር መግቢያ በር አድርጐ መግባት የሚያውቅበት ሰይጣን ወደ ሕዝቡ የሚቀርብበትን ምክንያት አገኘ። ቀርቦም «ኑ፥ ተከተሉኝና የሙሴን መቃብር ላሳያችሁ፤» አላቸው። እንዲህም ማለቱ ለእነርሱ አዝኖላቸው ሳይሆን፥ የሚሆንለት መስሎት፥ በሙሴ ሥጋ አድሮ ሊመለክ ፈልጐ ነው። ሕዝቡም እውነት መስሏቸው ተከተሉት። በዚህ ቅጽበት የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ከሰማይ ወርዶ ሰይጣንን ተቃወመው። «በቅዱሱ በሙሴ ሥጋ ማደር አትችልም፥ እርሱ የእግዚአብሔር ማደሪያ ነው፤» ብሎ ተከራከረው። በመጨረሻም ሦስት ጊዜ «እግዚአብሔር ይገሥጽህ፤» ቢለው ሰይጣን እንደ ትቢያ ተበትኖ ርቆላቸዋል። ይህ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ፍላጐታችንን ምክንያት አድርጐ ባልሆነ መንገድ እንዳይመራን ሰይጣንን ይቃወምልናል፥ ተከራክሮም ያሸንፍልናል ብለን እናምናለን። እንኳን በሕይወት እያለን ሞተንም በመቃብር ይጠብቀናል ብለን ተስፋ እናደርጋለን።
፩፥፱፦ በእስራኤል ሠራዊት ፊት ይሄድ የነበረው የእግዚአብሔር መልአክ፤ ዘጸ ፲፬፥፲፱
ከባርነት ቤት ከግብፅ የወጡትን ሕዝብ፥ እግዚአብሔር፦ ቀኑን በደመና ዓምድ፥ ሌሊቱን ደግሞ በብርሃን ዓምድ መርቷቸዋል። የግብፅ ንጉሥ ፈርዖን እስራኤልን «ሂዱ፤» ብሎ ከለቀቃቸው በኋላ መልሶ ስለጸጸተው ሠራዊቱን ይዞ ተከተላቸው። ፈርዖንም በቀረበ ጊዜ የእስራኤል ልጆች ዓይናቸውን አንሥተው ግብፃውያን ሲከተሉአቸው አዩ፤ እጅግም ፈርተው ወደ እግዚአብሔር ጮኹ። ምክንያቱም ሸሽተው እንዳያመልጡ ከፊት ለፊታቸው ያለው ባሕር ነው። በዚህ ላይ ፈርዖን ከነሠራዊቱ የተከተላቸው በፈረስ በሰረገላ በመሆኑ ሸሽተውም ቢሆን ማምለጥ አይችሉም። መሸሻ ሜዳ፥ መሸሎኪያ ቀዳዳ፥ መመከቻ ጋሻ፥ መሸሸጊያ ዋሻ አልነበራቸውም። ሙሴንም፦ «በግብፅ መቃብር ስላልኖረ በምድረ በዳ እንሞት ዘንድ አወጣኸንን? ከግብፅ ታወጣን ዘንድ ይህ ያደረግህብን ምንድነው? በምድረ በዳ ከምንሞት ብንገዛላቸው ይሻለናልና፦ ተወን፥ ለግብፃውያን እንገዛ፥ ብለን በግብፅ ሳለን ያልንህ ቃል ይህ አይደለምን?» አሉት። ሙሴም ለሕዝቡ «አትፍሩ፥ ዛሬ የምታዩአቸውን ግብፃውያንን ለዘለዓለም አታዩአቸውምና ቁሙ፤ (በእምነት ጽኑ)፤ ዛሬ ለእናንተ የሚያደርጋትን የእግዚአብሔርን ማዳን እዩ። እግዚአብሔር ስለ እናንተ ይዋጋል፥ እናንተም ዝም ትላላችሁ።» አላቸው። እግዚአብሔርም ሙሴን፦ «ለምን ትጮኽብኛለህ? ከብቶቻቸውን እንዲነዱ ለእስራኤል ልጆች ንገር። አንተም በትርህን አንሣ፥ እጅህንም በባሕሩ ላይ ዘርጋ፥ ክፈለውም፥ የእስራኤልም ልጆች በባሕሩ ውስጥ በየብስ ያልፋሉ። እነሆም እኔ የፈርዖንን እና የግብፃውያንን ልብ አጸናለሁ፥ በስተኋላቸውም ይገባሉ፤ በፈርዖንና በሰረገሎቹ፥ በፈረሰኞቹም ላይ እከብራለሁ። (ኃይሌን ገልጬ እመሰገናለሁ)። ግብፃውያንም በፈርዖንና በሰረገሎቹ፥ በፈረሰኞቹም ላይ ክብር ባገኘሁ (ኃይሌን ገልጬ በተመሰገንሁ) ጊዜ እኔ እግዚአብሔር እንደሆንሁ (ኃያልና ገናና ፈጣሪ መሆኔን) ያውቃሉ፤» አለው። በእስራኤልም ሠራዊት ፊት ይሄድ (ይመራቸው፥ ይጠብቃቸው) የነበረው የእግዚአብሔር መልአክ ፈቀቅ ብሎ በኋላቸው ሄደ፤ (ከፈርዖንና ከሠራዊቱ በክንፈ ረድኤቱ ጋረዳቸው)፤ የደመናውም ዐምድ ከፊታቸው ፈቀቅ ብሎ በኋላቸው ቆመ፥ በግብፃውያን ሰፈርና በእስራኤል ሰፈር መካከልም ገባ፥ በዚያም ጭጋግና ጨለማ ነበረ፤ ሌሊቱም አለፈ፥ ሌሊቱንም ሁሉ እርስ በርሳቸው አልተቃረቡም። ሲነጋም እግዚአብሔር አስቀድሞ እንደተናገረ በበትረ ሙሴ ላይ ኃይለ እግዚአብሔር ተገልጦ ባሕረ ኤርትራ ለሁለት ተከፈለ፥ ውኃው ግራና ቀኝ እንደ ግድግዳ ቆሞ፥ እስራኤል በደረቅ ተሻገሩ፥ ግብፃውያን ሰጥመው ቀሩ። ዘጸ ፲፬፥፩-፴፩።
እስራኤል ዘሥጋን በመንገዳቸው ሁሉ የጠበቃቸው፥ መና ከሰማይ ያወረደላቸው፥ ተአምራትን ያደረገላቸው፥ ማርና ወተት ወደምታፈስሰው ርስታቸው የመራቸው፥ በደመና መጋረጃ የጋረዳቸው፥ በክንፎቹም የሸፈናቸው መጋቤ ብሉይ የተባለ ቅዱስ ሚካኤል ነው። እኛንም ከዲያቢሎስና ከሠራዊቱ ይጠብቀናል፥ ከአሽክላው ይሰውረናል፥ ወደ ምድረ ርስት ገነት መንግሥተ ሰማያት ይመራናል፥ ብለን እናምናለን። ኅዳር አሥራ ሁለት ቀን በየዓመቱ በማኅሌት እና በቅዳሴ የምናከብረው ይኽንን ለእስራኤል ዘሥጋ የተደረገውን በማሰብ ነው። የበለጠው ደግሞ እስራኤል ዘነፍስ ለምንባል ክርስቲያኖች ይደረግልናል።
የእግዚአብሔር ቸርነት
የድንግል ማርያም አማላጅነት
 የሰባቱ ሊቃነ መላእክት የቅዱሳን የሰማእታት የቅዱሳን አባቶች ተራዳኢነት አይለየን ለዘላለሙ ወላአለም አለም አሜን

s.t yared


The Ethiopian and Egyptian sistrums are probably the oldest and best known idiophone types. Both are made of three or four metal rods that are horizontally drawn through a bow or U- shaped frame with a handle. They are of wood, porcelain, or pottery; the more recent standard type is made of metal. Both are equipped with movable discs, threaded on the rods, which jingle or clash when the instrument is shaken. It is interesting to note here that these ancient sistrums of African origin later spread to Greece, Rome, and other cultures around the Mediterranean as well as to other countries on the African continent. The sistrum used in Ethiopian Orthodox Christian Churches as well as in the Fellasha Synagogues are known as tsenatsil. Its social function is evidenced by its popularity in many Jewish Communities of North Africa, and the Middle and Near East, where it accompanies exclusively sacred chants. It is also interesting to indicate here that the four jingling metal bars on the sistrum are linked with the elements of nature: fire, water, air, and earth. In most of the cults, the sistrum was identified with votive power. The sistra of contemporary Ethiopia are strictly religious instruments played only by male deacons and priests to accompany sacred chants. In this case, close relationships exist.

Begena – a lyre with a box-shaped resonator
Embilta – a set of individual one-tubed end-blown pipes, each of a different size and name
Kebero – a large double-headed cylindrical drum made of a hollowed-out log
Kirar – a lyre with a bowl-shaped resonator
Masinqo – a bowed lute, a type of fiddle, with a diamond-shaped resonator
Tsenatsil – a sistrum made of three or four metal rods that are horizontally drawn through a bow or U- shaped frame with a handle        
The Tsenatsil is found in both Ethiopian and Jewish musical practices; in both cultures, it is played by male priests. Metallic idiophones had a universal role of protecting the bearer against evil spirits. In many oriental cultures of Africa and the Near East, for example, jingles are used in the rites of initiation and circumcision. This extra-musical roles associated and interrelated with magic and religion are by no means limited to the non-European world. It is also practiced in Europe; in A.D. 900, for example, Pope John IX ordered that bells be used in the Catholic Church as a defense against thunder and lightning. It is edifying to know the roles musical instruments play in religious, magical, and other symbolic services in societies, east and west.
According to gedle (biography), Ethiopia’s great ecclesiastic composer, poet, and priest, Saint Yared, was born in Axum ca. 496 (Ethiopian Calendar). Yared received educational and moral guidance from his uncle Gaidiwon who was then reputed to be a scholarly priest. Moreover, it is claimed that Yared was taken to Heaven where he was taught by three Holy Spirits, the arts of vocal performance, composition, poetry, versification and improvisation. Yared arranged and composed hymns for each season of the year, for summer and winter and spring and autumn, for festivals and Sabbaths, and for the days of the Angels, the Prophets, the Martyrs and the Righteous.
Mesmerized by the music, the Emperor accidentally dropped his spear into the flat part of Yared’s foot. Yared often sang for Emperor Gebre Meskel. “And when they heard the sound of his voice,” his Gedle (biography) tells us, “the king and the queen, and the bishop and the priests, and the king’s nobles, ran to the church, and they spent the day listening to him.” And one day Saint Yared sang in front of Emperor Gebre Meskel accompanied by drums, sistra, and male priests. Mesmerized by the music, the Emperor accidentally dropped his spear into the flat part of Yared’s foot. (See picture of Yared.) The Emperor was grieved by the pain he had inflicted on his spiritual friend. He said: “Ask me whatever reward thou wishest in return for this thy blood which hath been shed.” Yared made the Emperor promise that he would not refuse his request. Having accomplished that, Yared asked and was reluctantly granted permission to live in solitude and to dedicate his life to prayer, meditation, and to his music. He departed from Axum and went to the Semien mountains where he lived until his disappearance. According to our recent research among Ethiopian scholars, there is a general claim that he did not die, and that he will come back in the future to perform, preach, and teach. He was sainted after his disappearance.
One day Saint Yared sang in front of Emperor Gebre Meskel accompanied by drums, sistra, and male priests.

Glory be to God Who is glorified in His Saints.amen

ሰማእቷ ቅድስት አርሴማ


     በአብ ስም አምኜ፣ አብን ወላዲ ብዬ፣ በወልድ ስም አምኜ፣ ወልድን ተወላዲ ብዬ፣ በመንፈስ ቅዱስ ስም አምኜ መንፈስ ቅዱን ሰራጺ ብዬ በማመን፤ ምንም እንኳን ለአጠይቆ አካል ሦስት ብልም፤ ዓለምን በመፍጠር፣ በማሳለፍ፣ በባህሪይና በህልውና አንድ አምላክ ብዬ በማመን የእመቤታችን የቅድስተ ቅዱሳን የድንግል ማርያምንና የቅዱሳንን ሁሉ አማላጅነት አጋዥ በማድረግ አምላክ ቅዱሳን ያቃበለኝን ያህል ስለ እምነት አርበኛዋ ቅድስት አርሴማ ትንሽ እናገራለሁ።

“በእሳት ተቃጥለው በውሃ ተቀቅለዋል፤ በሰይፍ ተመትረዋል፤ በመጋዝ ተተርትረዋል፤ በመንኩራኩር ተፈጭተዋል፤ እንደ ከብት ቆዳቸው

ተገፈዋል። ወደ ጥልቅ ባሕር ተጥለዋል። በዚህ ሁሉ ከሃይማኖታቸው አላፈገፈጉም።”

   የሰማዕቷ ምልጃ ፀሎት እና በረከቷ ከሁላችን ጋር ጸንቶ ለዘላለሙ ይኑር አሜን !!!!

  ቅዱሳን ሰማዕታት 
 ቅዱሳን ሰማዕታት ማለት “እግዚአብሔርን ካዱለጣዖት ስገዱ፤ሲባሉ እግዚአብሔርን አንክድም ለጣዖት አንሰግድም፤” በማለት በዓላውያን ነገስታት ፊት ቀርበው ሳያፍሩና ሳይፈሩ ስለ ፈጣሪያቸውን የመሰከሩ ናቸው። በዚህም ምክንያት ተዘርዝሮ የማያልቅ የመከራ ዓይነት
ተቀብለው ለእግዚአብሔር ለፈጣሪያቸው ክብር ሲሉ ደማቸውን ያፈሰሱ፣ አጥንታቸውን የከሰከሱ ሕይወታቸውንም የሰጡ ናቸው። በእሳት ተቃጥለው በውሃ ተቀቅለዋል፤ በሰይፍ ተመትረዋል፤ በመጋዝ ተተርትረዋል፤ በመንኩራኩር ተፈጭተዋል፤ እንደ ከብት ቆዳቸው ተገፈዋል። ወደ ጥልቅ ባሕር ተጥለዋል። በዚህ ሁሉ ከሃይማኖታቸው አላፈገፈጉም። ለዚህ ነው፡- በዕብራውያን ፲፫፡፯ (13፡7) ላይ “የእግዚአብሔርን ቃል የተናገሩአችሁን ዋኖቻችሁን አስቡ፥ የኑሮአቸውንም ፍሬ እየተመለከታችሁ በእምነታቸው ምሰሉአቸው።” የተባለው።
በተጨማሪም ጌታ እራሱ በዚህ በራዕይ ፪፡፲ (2፡10) ላይም እንዲህ ሲል ተናግሯል፤ “ልትቀበለው ያለህን መከራ አትፍራ።እነሆ፥ እንድትፈተኑ ዲያብሎስ ከእናንተ አንዳንዶቻችሁን በወኅኒ ሊያገባችሁ አለው፥ አሥር ቀንም መከራን ትቀበላላችሁ። እስከሞት ድረስ የታመንህ ሁን የሕይወትንም አክሊል እሰጥሃለሁ።” ብሏል። በይሁዳ ፩፡፫ (1፡3) ላይም “ወዳጆች ሆይ፥ ስለምንካፈለውስለ መዳናችን ልጽፍላችሁ እጅግ ተግቼ ሳለሁ፥ ለቅዱሳን አንድ ጊዜ ፈጽሞ ስለ ተሰጠ ሃይማኖት እንድትጋደሉ እየመከርኋችሁ እጽፍላችሁ ዘንድ ግድ ሆነብኝ።” ይላል።


  ስለ ሰማዕቷ ቅደሰት አርሴማ ትነሽ ልበላችሁ.....
የጎርጎርዮስ ዘአርመንያ እኀት ናት። ዲዮቅልጥያኖስ ቆንጆ ሴት ፈልጋችሁ ስዕሏን ስላችሁ አምጡልኝ ብሎ ሰራዊቱን በየሀገሩ ሰደደ። ይሀቸ አርሴማ ከ71 ደናግለ ጋር ከተራራ ወጥታ ተቀምጣ ነበር። እየፈለጉ ሲሄዱ እሷን አይተው ስዕሏን ስለው ወስደው ሰጡት። መልካም ብላቴና አግኝታችሁልኛል ሄዳችሁ አምጡልኝ አላቸው። እርሷም አውቃ አርመንያ ወረደች፤ ይህን ሰምቶ ለንጉስ ለድርጣድስ አስፈልገህ ላክለኝ ብሎ ላከበት፤ አስፈልጎ አገኛት። እርሱም መልከ ቀናነቷን አይቶ ይህችንስ አሳልፌ አልሰጥም ብሎ መሪያቸው ‘ደርታን’ ለምኝልኝ አላት። አይሆንምያልሁ እንደሆነ ጸብ አጸናለሁ ብላ እሺ አለችው። እሷን ግን ለመንግስተ ሰማያት የታጨሽ ነሽና ይህ ዕልው እንዳያረክስሽ እወቂ አለቻት። ከዚህ በኋላ ጽዋት ልኮ ወሰዳት፤ መልኳን አይቶ በስሜት ተሸንፎ ዘሎ ያዛት። ኃይለ መንፈሳዊ ተሰጥቷታልና ጎትታ ከመሬት ቀላቀለችው። ንጉስ ነውና ቢያፍር በሰይፍ አስመታት፤ ከዚህም አያይዞ ‘ሰባ አንዱንም’ ሁሉ በሰይፍ አስመትቷቸዋል። በወንጌል ላይ “እነርሱ በእምነት መንግሥታትን ድል ነሡ፥ ጽድቅን አደረጉ፥ የተሰጠውን የተስፋ ቃል አገኙ፥ የአንበሶችን አፍ ዘጉ፥ የእሳትን ኃይል አጠፉ፥ ከሰይፍ ስለት አመለጡ፥ ከድካማቸው በረቱ፥ በጦርነት ኃይለኞች ሆኑ፥ የባዕድ ጭፍሮችን አባረሩ። ሴቶች ሙታናቸውን በትንሣኤ ተቀበሉ፤ ሌሎችም መዳንን ሳይቀበሉ የሚበልጠውን ትንሣኤ እንዲያገኙ እስከ ሞት ድረስ ተደበደቡ፤ ሌሎችም መዘበቻ በመሆንና በመገረፍ ከዚህም በላይ በእስራትና በወኅኒ ተፈተኑ፤ በድንጋይ ተወግረው ሞቱ፥ ተፈተኑ፥ በመጋዝ ተሰነጠቁ፥ በሰይፍ ተገድለው ሞቱ፥ ሁሉን እያጡ መከራን እየተቀበሉ እየተጨነቁ የበግና የፍየል ሌጦ ለብሰው ዞሩ፤ ዓለም አልተገባቸውምና በምድረ በዳና በተራራ፥ በዋሻና በምድር ጕድጓድ ተቅበዘበዙ።” ዕብ.፲፩፡ ፴፫-፴፰ (11፡33-38 ያለው ይፈጸም ዘንድ ይህን ሁሉ መከራ ተቀበሉ። ኋላ ግን መልኳ ትዝ እያለው እህል ውሃ የማይቀምስ ሆነ። ወዳጆቹ ነገሩን እንዲረሳ ብለው አደን ይዘውት ወጡ። በዚያ እሪያ ሆኖ ቀርቷል። የንጉሱ እህት ጎርጎርዮስን ወንድሜን አድንልኝ ስትለው አጽመ ቅዱሳንን አሳዩኝ ብሎ አሳይታው ያን አስቀብሮ ካለበት ሄዶ “ባድንህ በፈጣሪ ታምናለህ?” አለው።እርሱም በአዎንታ እራሱን ነቀነቀ። የተደረገለትን እንዳይዘነጋ ከእጁ ከእግሩ የእርያ ምልክት ትቶ ጸልዮ አድኖታል። ኋላም አምኛለሁ አጥመቀኝ በማለቱ ቢጠይቀው ሥልጣን የለኝም አለው፤ በአንጾኪያው ሊቀ ጳጳስ እጅም ተጠመቀ። እርሱንም ሊቀ ጳጳስነት አስሹሞ ብዙ ተግሳጻትን ጽፎ ብዙ ድርሳናትን ደርሶ ብዙ የቱርፋት ሥራ ሠርቶ አርፏል።እረፍቱም ታህሳስ 15 ቀን ነው። ቅድስት አርሴማ ግን በዚህ ሁሉ ተጋድሎዋ እግዚአብሔር የገባላት ቃል ኪዳን በእኔ ስም አምነሽ የዚህ ዓለም ተድላና ደስታ ሳያታልልሽ አንገትሽን ለሰይፍ ሰጥተሽ ተሰይፈሻል፤ የሰማዕትነት ተጋድሎ ፈጽመሻልና ስምሽን የጠራ፤ በዓልሽን ያከበረ፤ ዝክርሽን የዘከረ፤ ገድልሽን የጻፈና ያጻፈ፤ የሰማና ያሰማም እስከ ፲፪ ትውልድ ድረስ እምርልሻለሁ’’ ሲል ቃል ኪዳን ገብቶላታል፡፡ በዚህም መሠረት በሷ አማላጅነት አምኖ ገዳሟም ሄዶ በጸሎት የተማጸናት ሁሉ ለችግሩ መፍትሄ አግኝቶ እንደሚመለስ እሙን ነው። የሰማዕቷ ረድኤት በረከት ይጠብቀን አሜን፡፡

  ካለመኖር ወደ መኖር ያመጣኝ፣ ካለማወቅ ወደ መረዳት ያደረሰኝ አነሳስቶ ላስጀመረኝ አስጀምሮ ላስፈጸመኝ ጥንት ላሌለው ቀዳማዊ ፍጻሜ ላሌለው ድህራዊ ያልኖረበት ጊዜ የሌለ የማይኖርበት ጊዜም የማይኖር የዘላለም ንጉስ ሁሉን ቻይ ፈጣሪ እግዚአብሔርን በራስ ፀጉሬ ቁትር በአጥንቶቼም ልክ አመሰግናለሁ፡፡ እድሜ ለንሰሐ ዘመን ለፍሰሃ ሰጥቶኝ ይህችን ታህል ስለ አባታችን እንድመሰክር የረደኝ አምላክ ስሙ የተመሰገነ ይሁን።

  አመስግኛት የማልሰለች፣ ስለሷ ተናግሬ የማይደክመኝ፣በሰማይ ያሉ መላእክት በምድርም የሚኖሩ የአዳም ዘር ሁሉ የሚያመሰግኗት በአማላጅነቷ ሁል ጊዜ የማትለየኝ ከፀሐይ ሰባት እጅ የምታበራ የብርሃን እናት የሁሉ እመቤት የአምላክ እናት ከተመረጡ የተመረጠች ከተለዩ የተለየች ከተከበሩ የተከበረች እናቴ እመቤቴ ድንግል ማርያም በቃላት ልገልጸው ከምችለው በላይ አመሰግናለሁ፡፡

  የእግዚአብሔር፣ቸርነት የድንግል ማርያም አማላጅነት፣ የቅዱሳን መላእክት ተራዳኢነት፣ የጻድቃን፣ የሰማዕታት፣ የቅዱሳን ሐዋርያት፣ የቅዱሳን አበው መነኮሳት፣ የቅዱሳት አንስት፣ የደናግላንና የቅዱሳን ሁሉ ምልጃና ቃል-ኪዳናቸው ባለንበት ከሁላችን ጋር ይሁን ይቆየን፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ለዘበቅዱሳኒሁ ይሴባሕ ይእዜኒ ወዘልፈኒ ወለዓለም ዓለም አሜን፡፡ ወአሜን ለይኩን ለይኩን፡፡ አነሳስቶ ያስጀመረኝ አስጀምሮ ያስጨረሰኝ የቅዱሳን አባቶቻችን አምላክ ይክበር ይመስገን አሜን፡፡ ምንጭ፡- ነገረ ቅዱሳን ቁ.፩፣ መዝገበ ታሪክ ቁ.፩፣ ስንክ ሳር ዘታህሳስ መልከአ ቅ/አርሴማ

አቡነ ዜና ማርቆስ


   በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን
አቡነ ዜና ማርቆስ በ፲፫ኛ/13ኛው/ መቶ ክ/ዘመን)
ስለ እመቤታችን፣ ስለሐዋርያት፣ ስለነገስታት፣ ስለጻድቃን፣ ስለሰማዕታት፣ ስለ ቅዱሳን መላእክት በአጠቃላይ ስለ ቅዱሳን ሁሉ እንወቅ፣ እንመርምር፣ እንጠይቅ፣እንማማር ለዚህም እግዚአብሔር አምላክ እዝነ ልቦናችንን ይክፈትልን፤ የአዲስ ኪዳን ኪሩብ የጸጋ መፍሰሻ ምልዕተ ክብር ምልዕተ ውዳሴ የሆነች እመቤታችን ድንግል ማርያም ምስጢር ትግለጥልን አሜን!!!
† ቅዱሳን ጻድቃን መላ ዘመናቸውን ከጣዕመ

ዓለምና ከተድላ ዓለም ተለይቶ ቤት ልስራ ዘር ልዝራ ሳይሉ ፈቃደ ሥጋቸውን ለፈቃደ ነፍሳቸው አስገዝተው በጾም፣ በጸሎት፣ በስግደት፣ በምናኔ ጸንተው የኖሩ ናቸው።
ቅዱስ አባታችን አቡነ ዜና ማርቆስ ገራቸው ዞረሬ /ጽላልሽ/ ነው። አባታቸው ካህን ዮሃንስ የጻድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖት አባት የአቡነ ጸጋዘአብ ወንድም ነው። እናታቸው ዲቦራ (ማርያም ዘመዳ ትባላለች። የአቡነ ቀዎስጦስ እህት ናት። በብስቃረ ማርቆስ ወንጌላዊ ህዳር ፳፬ /24/ ተወልዷል። አርባ ቀን ሲሞላው ሊያስጠምቋቸው ቤተ ክርስቲያን ወሰዷቸው። ጸሎተ ጥምቀቱ ደርሶ ከውሃ ውስጥ ሲከቷቸው ቆመው እሰግ ለአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ብለው 3 ጊዜ ሰግዶአል። ውሃው ፈላ አጥማቂው ቄስ የጻድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖት አባት የአቡነ ጸጋዘአብ ወንድም ካህኑ እንድርያስ ነበር። እድሜው 72 ዓመት ስለነበር በሕፃኑ ድርጊት ፈርቶ ወደ ቤተ መቅደስ ሮጠ። ቅዱስ ሩፋኤ ከፍርሃቱ አጽናንቶት ከማየ ጸሎቱ ራሱን እንዲቀባ ነግሮት በራ የነበረ ራሱ ጸጉር በቅሎለታል።አቡነ ዜና ማርቆስ 5 ዓመት ሲሞላቸው ወላጆቻቸው ለመምህር ሰጧቸው። በ 3 ዓመት ብሉይንና ሐዲስ አጥንተው በ8 ዓመታቸው ከቅዱስ ቄርሎስ ድቁና ተቀብለው ሲመጡ ሽፍቶች የእጃቸውን በትር ነእሳቸውም ወደ ጌታ ቢያመለክቱ በትራቸው እባብ ሆና ነድፋ ገድላቸዋለች። 30 ዓመት ሲሆናቸው ማርያም ክብራ ለምትባል ደግ ሴት አጋቧቸው። ልማደ መርዓዊ ወመርዓት (ሙሽራውና ሙሽራይቱ) ያድርሱ ብለው መጋረጃ ሲጥሉባቸው በሌሊት ወጥተው ሄዱ። መልአኩ ቅዱስ ሩፋኤል ሀገረ ምሑር አድርሷቸውዋል። በዛም የኢየሱስ ክርስቶስን ስም በመጥራታቸውና ከንጉሱ (ሀገረ ገዢው) አብላኝ በማለታቸው የኔ አምላክ ማኮስ ነው ኢየሱስ የምትለው ማን ነው ቢላቸው አምላካችን ነው ቢሏቸው ወስዶ ቤተ ጣዖት ቢያሳያቸው ወስደው በእግር ረግጠው አሰጠሙት። መስፍኑ ተቆጥቶ አሰራቸው። መልአኩም ከእስራታቸው ፈቷቸዋል። እንዲያበላቸው ዳግም ሀገረ ገዢውን ቢጠይቁት ተናዶ በጦር ሊወጋቸው ሲል ምድር አፏን ከፍታ ባሕር ሆና አሰጠመችው። እንዲህ እያሉ ብዙ ስለ ጌታ መስክረዋል።
ኋላም ወደ ምድረ ጉራጌ ወርደው ብዙውን አስተምረው ወደ እምነት መልሷል። ብዙዎችም አሳምነው አጥምቋቸዋል። በጸሎታቸውም ብዙ በሽተኞችን ፈውሶ የትሩፋት ሥራን ሠርተዋል። ሃላም አቡነ ተክለ ሃይማኖት ምንኩስና ሰቷቸው ወደ ደብረ አስቦ (በደ/ሊባኖስ ተክልዬ ለ29 ዓመታት የጸለዩበት ቦታ) ሄዱ። ከዚህ በኋላ አቡነ ዜና ማርቆስ ደብረ ብስራትን ገድመው እያስተማሩ ኖረው ፪፻ አናብስት በ፪፻ አናምርት ታጅበው በደመና ተጭነው ብዙ ቦታ በመሄድ አስተምረው አሳምነዋል። ከእረፍታቸው በፊትም ልጆቻቸውን በሙሉ ከየ ሀገሩ ጠርተው ቅዳሴ ቀድሰው ሲያቆርቡ ከብዛታቸው የተነሳ ፀሐይ ልትገባ ስለሆነ ወደ ጌታ አመልክተው አቀብለው እስኪፈጽሙ ድረስ ፀሐይ ባለችበት እንድትቆም አድርገዋል። ከዚህ የበዙ ተዓምራትን ሲያደርጉ ኖረው በተስፋቸው ያመነ በኪዳናቸው የተማጸነ ዋጋውን እንደማያጣ ጌታ ቃል ኪዳን ሰጥቷቸው በተወለዱ በ፻፬ (140) ዘመናቸው ታህሳስ ፫/ 3/ ቀን ዐርፈዋል።
† የቅዱሳን አኗኗራቸው ድምጸ አራዊቱን ጸብዓ አጋንንቱን ግርማ ሌሊቱን ሳይሳቀቁ ደዋ ጥሰው፣ ደንጋይ ተንተርሰው፣ ጤዛ ልሰው ነው። ይህን ነው ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ “ሁሉን እያጡ መከራን እየተቀበሉ እየተጨነቁ የበግና የፍየል ሌጦ ለብሰው ዞሩ፤ዓለም አልተገባቸውምና በምድረ በዳና በተራራ፥ በዋሻና በምድር ጕድጓድ ተቅበዘበዙ።” † በማለት በዕብ.11፡37-38። በረከትና ቃል ኪዳናቸው በምልጃቸው ከምናምን ሕዝበ ክርስቲያን ጋር ለዘላለሙ ጸንቶ ይኑር አሜን።
+ ካለመኖር ወደ መኖር ያመጣኝ፣ ካለማወቅ ወደ መረዳት ያደረሰኝ አነሳስቶ ላስጀመረኝ አስጀምሮ ላስፈጸመኝ ጥንት ላሌለው ቀዳማዊ ፍጻሜ ላሌለው ድህራዊ ያልኖረበት ጊዜ የሌለ የማይኖርበት ጊዜም የማይኖር የዘላለም ንጉስ ሁሉን ቻይ ፈጣሪ እግዚአብሔርን በራስ ፀጉሬ ቁትር በአጥንቶቼም ልክ አመሰግናለሁ፡፡
+ በሰማይ ያሉ መላእክት በምድርም የሚኖሩ የአዳም ዘር ሁሉ የሚያመሰግኗት በአማላጅነቷ ሁል ጊዜ የማትለየኝ ከፀሐይ ሰባት እጅ የምታበራ የብርሃን እናት የሁሉ እመቤት የአምላክ እናት ከተመረጡ የተመረጠች ከተለዩ የተለየች ከተከበሩ የተከበረች እናቴ እመቤቴ ድንግል ማርያም በቃላት ልገልጸው ከምችለው በላይ አመሰግናለሁ፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር ለዘበቅዱሳኒሁ ይሴባሕ ይእዜኒ ወዘልፈኒ ወለዓለም ዓለም አሜን፡፡ ወአሜን ለይኩን ለይኩን፡፡

መላእኩ ቅዱስ ዑራኤል



በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን::
በፍጹም መጠበቅን ጠብቆ ለዚህ ያደረሰን አምላካችን ክብርና ምስጋን አምልኮትና ውዳሴ ይድረሰውና ይህን ታላቅ መልአክ በችሎታችን መጠን እንድናመሰግን እግዚአብሔር ይርዳን፤ አምላክ ባለንበት ከሁላችን ጋር ይሁን፤ ምስጢሩን ይግለጥልን አሜን፡፡

“ዑራኤል የተባለ መልአክ ሊረዳኝ መጣ፡፡” መ/ዕዝ. ሱቱ. 2፡1
በመንገድህ ሁሉ ይጠብቁህ ዘንድ መላእክቱን ስለ አንተ ያዝዛቸዋልና፤ እግርህም በድንጋይ እንዳትሰናከል በእጆቻቸው ያነሡሃል።
በተኵላና በእባብ ላይ ትጫማለህ፤ አንበሳውንና ዘንዶውን ትረግጣለህ ::
  በእኔ ተማምኖአልና አስጥለዋለሁ፤ ስሜንም አውቆአልና እጋርደዋለሁ። ይጠራኛል እመልስለትማለሁ፥ በመከራውም ጊዜ ከእርሱ ጋራ እሆናለሁ፤ አድነዋለሁ አከብረውለሁ። ረጅምን ዕድሜ አጠግበዋለሁ፥ ማዳኔንም አሳየዋለሁ። መዝ. 90/91/፡11-16


አፈቅሮ ፈድፋደ፡- ዑራኤል ሆይ፣ ከመልኮች ሁሉ ይልቅ ያንተን መልክአ ጸሎት እወዳለሁ፡፡ የመልክህ ስነ ጸዳል በደመ ወልድ እግዚአብሔር የታተመ ነውና፡፡
ዑራኤል ሆይ፣ እግዚአብሔር ሀይሉን የሚገልጽብን መልአከ ብርሃናት አንተ ነህ፡፡ በዐለተ ሥቅለት በደመ ወልድ ዓለምን ለመቀደስ ከሁሉ ይልቅ አንተ ተሰይመሃልና፡፡ ስለክብርህ የሰማይ መላእክት አደነቁ፡፡

ለተፈጥሮትከ፡-
ዑራኤል ሆይ፡- ያለ መናገር በጥንት አርምሞ ከነፋስና ከእሳት ለተፈጠረ ተፈጥሮህ ሰላም እላለሁ፡፡ ዑራኤል ሆይ የተፈጥሮና የይቅርታና የቸርነት ክቡር መልአክ ነህና ስለኛ ስለሰው ልጆች ወደ ልዑል እግዚአብሔር ማልድ አማላጅነትህ ዘወትር ከጥፋት ያድናልና፡፡

ለዝክረ ስምከ፡-

ዑራኤል ሆይ፡- ከማርና ከወተት ይልቅ ለሚጥመው ስም አጠራርህ ሰላም እላለሁ፡፡

ዑራኤል ሆይ፡- ክፍልህ /ክንፍህ/ በደመ ወልድ እግዚአብሔር የተከበረ /የታለለ/ ነውና፡፡ ለዓለሙ ሁሉ መድሃኒት ትሆን ዘንድ ግሩም የሚሆን የእግዚአብሔር ሥልጣን በክብር ከፍ ከፍ አደረገ፡፡ (መልክአ ዑራኤል)

“የእግዚአብሔር መልአክ በሚፈሩት ሰዎች ዙሪያ ይሰፍራል፥ ያድናቸውማል።” መዝ.33/34/፡7 የሊቀ መልአኩ የክዱስ ዑራኤል ረድኤቱ በረከቱ ፍጹም አማላጅነቱ ከሁላችን ጋር ይሁን፡፡

ካለመኖር ወደ መኖር ያመጣኝ፣ ካለማወቅ ወደ መረዳት ያደረሰኝ አነሳስቶ ላስጀመረኝ አስጀምሮ ላስፈጸመኝ ጥንት ላሌለው ቀዳማዊ ፍጻሜ ላሌለው ድህራዊ ያልኖረበት ጊዜ የሌለ የማይኖርበት ጊዜም የማይኖር የዘላለም ንጉስ ሁሉን ቻይ ፈጣሪ እግዚአብሔርን በራስ ፀጉሬ ቁትር በአጥንቶቼም ልክ አመሰግናለሁ፡፡

በሰማይ ያሉ መላእክት በምድርም የሚኖሩ የአዳም ዘር ሁሉ የሚያመሰግኗት በአማላጅነቷ ሁል ጊዜ የማትለየኝ ከፀሐይ ሰባት እጅ የምታበራ የብርሃን እናት የሁሉ እመቤት የአምላክ እናት ከተመረጡ የተመረጠች ከተለዩ የተለየች ከተከበሩ የተከበረች እናቴ እመቤቴ ድንግል ማርያም በቃላት ልገልጸው ከምችለው በላይ አመሰግናለሁ፡፡ ሌሊትና ቀን ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ እያሉ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔርን የሚያመሰግኑና ሳይሰለቹ የሚጠብቁን ሊቀነ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ቅዱስ ገብርኤል ቅዱስ ሩፋኤል ቅዱስ ዑራኤል ቅዱስ ራጉኤል ቅዱስ ፋኑኤል እልፍ አእላፋት የሆኑ ጠባቂ መላእክት ሳመሰግን በደስታ ነው፡፡
በጸሎታቸው ያልተለዩኝን ጻድቃን አባቶቼን አቡነ ተክለሃይማኖትን አቡነ ገብረምንፈስ ቅዱስን አቡነ ሀብተማርያምን አቡነ አረጋዊን አቡነ ኪሮስንና ሌሎች ቅዱሳን አባቶቼን እንዲሁም እናቶቼን ቅድስት ክርስቶስ ሰምራን ቅድስት አርሴማን ብዙ ያልጠቀስኳቸው ቅዱሳንን ለማመስገን ቃላት የለኝም፡፡
በሰማኝትነታቸው የጥንካሬ ምሳሌ የሆኑልኝ በጸሎታቸው የረዱኝን ቅዱሳን ሰማዕታት ቅዱስ ጊዮርጊስን ቅዱስ እስጢፋኖን መጥመቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስንና ሌሎችን ቅዱሳን ሰማዕታትን ሁሉ በእጅጉ አመሰግናለሁ ለዘላለሙ አሜን፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር ለዘበቅዱሳኒሁ ይሴባሕ ይእዜኒ ወዘልፈኒ ወለዓለም ዓለም አሜን፡፡ ወአሜን ለይኩን ለይኩን፡፡

እምሊባኖስ ትወፅእ መርዓት

እምሊባኖስ ትወፅእ መርዓት

ኦ ድንግል አኮ በፍተወተ ደነስ ዘተጸነስኪ ፡፡ ድንግል ዘርዕ ዘይወጽእ እምስካበ ተዓዳዌ ሕግ ይከውን ለቅጥቃጤ ወለሙስና ባለው ፈቃድ የተፀነሽ አይደለሽም፡፡ አላ በሩካቤ ዘበህግ እምሐና ወኢያቄኒም ተወለድኪ ክቡር አውስቦ በኵለሄ ወለምስካቦሙኒ አልቦቱ ስዕበት ባለው ፈቃድ ከሐና ከኢያቄም ተወለድሽ እንጂ፡፡ አንድም እስመ ናሁ በኃጢአት ተፀነስኩ፡፡ ወበአመፃ ወለደተኒ እ...ምየ እንዲል፡፡ በልተው ጠጥተው በሚያደርጉት ፈቲው ጽነት የተፀነስሽ አይደለም፡፡ ብዝኁ ወተባዝኁ ባለው ፈቃድ ከሐና ከኢያቄም ተወለድሽ እንጂ፡፡ ታሪክ የእመቤታችን ቅድመ አያቶቿ ቴክታ በጥሪቃ ይባላሉ፤ ይህ ቀራቸው የማይባሉ ባለጸጎች ነበሩ ፤ ብእላቸውም የወርቅ ፤ የብር የፈረስ ፤ የበቅሎ የሴት የባርያ የወንድ ባርያ ነው፡፡ ከወርቁ ብዛት የተነሳ እንደ አምባር እንደ ቀለበት እያሠሩ ከበሬው ከላሙ ቀንድ ያደርጉት ነበር፡፡ ይህን ያህል አቅርንተ ወርቅ ይህን ያህል አቅርንተ ብሩር ተብሎ ይቆጠር ነበር እንጂ የቀረው አይቆጠርም ነበር፡፡ ከእለታት ባንዳቸው ከቤተ መዛግብት ገብቶ የገንዘቡን ብዛት አይቶ ቴክታ እኔ መካን’ አንቺ መካን ይህ ሁሉ ገንዘብ ለማን ይሆናል አላት እግዚአብሔር እንጂ ከኔ ባሰጥህ ወይ ከሌላ ይሰጥህ ይሆናል ፤ አግብተህ አትወልድምን አለችው ይህስ እንዳላደርገው አምላከ እስራኤል ያውቃል አላት፤ በዚህ ጊዜ አዘኑ ወዲያው ራእይ አይተዋል ፤ ነጭ እንቦሳ ከበረታቸው ስትወጣ ፤ እንቦሳቱ እንቦሳ እየወለደች እስከ ስድስት ስትደርስ ፤ ስድስተኛዪቱ ጨረቃን ጨረቃ ፀሐይን ስትወልድ አይተው በሃገራቸው መፈክረ ሕልም አለና ሂደው ነገሩት ፤ ደግ ልጅ ትወልዳላችሁ ፤ ጨረቃይቱ ከፍጡራን፡፡ በላይ የምትሆን ልጅ ትወልዳላችሁ የፀሐይ ነገር ግን አልተገለጸልኝም አንደ ነቢይ አንደ ንጉሥ ያለ ይሆናል አላቸው ጊዜ ይተርጉመው ብለውት ሄዱ፡፡ ከዚህ በኋላ ፀነሰች ፤ ወለደች ስሟን ሄኤሜን ዴርዴን ዴርዴ ቶናን ቶና ሲካርን ሲካር ሄርሜላን፤ ሄርሜላ ሐናን ወለደች፡፡ ሐና አካለ መተን ስታደርስ ከቤተ ይሁዳ ለተወለደ ኢያቄም ለሚባል ደግ ሰው አጋቧት ፤ ምክነት ወርዶ እንደ አያቶችዋ ሁናለች ብዕሉ ግን በመጠን ሁኑዋል፡፡ ከጎረቤትዋ በዝሙት የምትኖር አንዲት ሴት ነበረች ሐና ዛሬ ቤተ ክርስቲያን እስማለሁ ብዬ ነበር፤ ነገር ግን የምለብሰው ልብስ የለኝም አለቻት፤ እርሱዋም ልብስማ የኔ ካንድ ሁለት ሦስት ልብስ ያለልሽ አይደለም የንን ለብሰሽ አትሄጅም አለቻት፡፡
ያንቺ ልብስ የተሰበሰበ በዐስበ ደነስ በዐስበ ዝሙት ነው፡፡ እግዚአብሔር ንጹሐ ባሕርይ ነው ንጹሕ ነገር ይወዳል ይህን ለብሼ ብለምነው ምን ይሰማኛል ብየ ነዋ አለቻት ሐና እኔ በምን ምክንያት ልጅ ነሳት እያልሁ ሳዝንልሽ እኖር ነበር ለካ አንደ ደንጊያ አድርቆ ያስቀረሽ ይህ ክፋትሽ ነው አለቻት ፤ በዚህ አዝናለች፡፡ አንድም ሁለቱ ሁሉ መሥዋዕት እናቀርባለን ብለው ከቤተ መቅደስ ሄዱ፤ ሊቀ ካህናቱ ሮቤል ይባል ነበር ወይትዌከፍ መሥዋእቶሙ ለመካናት እንጀ ይላል፤ እናንተማ ብዙኁ ወተባዝኁ ብሎ ለአዳም የነገረውን ያስቀረባችሁ ርጉማን አይደላችሁምን ቢጠላችሁ አልነበረምን መሥዋዕታችሁን አልቀበልም ብሏቸው በዚህ እያዘኑ ተመልሰዋል፡፡ አንድም ከአዕሩግ እስራኤል የተወለዱ ሰዎች የሚመገቡት ተረፈ መሥዋእት ነበር ያነን ነስቷቸው እያዘኑ ሲመለሱ ከዛፍ ስር ተቀምጠው አርጋብ ከልጆቻቸው ጋራ ሲጫወቱ ዕፅዋት አብበው አፍርተው አይታ አርጋብን በባሕርያቸው እንዲራቡ ዕፅዋትን አንዲያብቡ እንዲያፈሩ የምታደርግ የኔ ተፈትሮዬ ከደንጊያ ይሆን ልጅ የነሳኸኝ ብላ አዘነች ከቤታቸው ሂደው ወንድ ልጅ ብንወልድ ወጥቶ ወርዶ አርሶ ቆፍሮ ርዳን አንልም ፤ ለቤተ እግዚአብሔር አንጣፊ ፤ ጋራጅ ሁኖ ይኖራል ሴት ብንወልድ ዕንጨት ሰብራ ውኃ ቀድታ ትርዳን አንልም ለቤተ እግዚአብሔር በሶበ ወርቅ ሰፍታ መጋረጃ ፈትላ ትኑር ብለው ብፅአት ገብተዋል የሐምሌ አመ ፴ ዕለት እሷ ለሱ ፀምር ሲያስታጥቁህ መቋምያህ አፍ አፍርታ ፍጥረት ሁሉ ሲመገብ አየሁ ብላ እሱ ለሷዋ ጸዓዳ ርግብ ሰባቱን ሰማያት ሰንጥቃ መጥታ በራስሽ ላይ ስታርፍ በቀኝ ጆሮሽ ገብታ በማሕጸንሽ ስታድር አየሁ ብሎ ያዩትን ሕልም ተጨዋውተዋል፡፡ በሀገራቸው መፈክረ ሕልም አለና ሂደው ነገሩት ደግ ልጅ ትወልዳላችሁ አላቸው ፤ አንተስ አልፈታኸውም ጊዜ ይፍታው በወለው ተመልሰዋል፡፡ በነሐሴ ሰባት ቀን መልአክ መጥቶ ደግ ልጅ ትወልዳላችሁ ብሏቸው በብስራተ መልአክ በፈቃደ አምላክ እመቤታችን ተፀነሰች፡፡ በተፀነሰችም ጊዜ ብዙ ተአምራት ተደርጓል፤ በርሴባ የምትባል አክስት ነበረቻት አንድ ዐይና ነች ፤ ሐና እግዚአብሄር በረድኤት ጎበኘሽ መሰለኝ ጡትሽ ጠቁሯል ከንፈርሽ አሯል ብላ ማኅፀኑዋን ዳሳ ዐይኑዋን ብታሸው በርቶላታል፣ ይህን አብነት አድርገው ሕሙማን ሁሉ ማኅፀኑዋን እየዳሰሱ የሚፈወሱ ሆነዋነዋል፡፡
ዳግመኛምሳምናስ የሚባል ያጎትዋ ልጅ ነበር ሞተ፤ ትወደው ስለነበርና ያለጋውን ሸንኮር ይዛ እየዞረች ስታለቅስ ጥላዋ ቢያርፍበት ተነስቶ ሰላም ለኪ ኦ እምሔውቱ ለዘገብረ ሰማየ ወምድረ ብሎ ከበፈክረ ሕልም የቀረውን ተርጉሞታል፡፡ ከዚህ በኋላ አይሁድ ለምቀንነት አያርፉምና ቀድሞ ከነዚህ ወገን የሚሆኑ ዳዊት ሰሎሞን አርባ አርባ ዘመን እንደ ሰም አቅልጠው አንደ ገል ቀጥቅጠው ገዙን፡፡ ደግሞ ከዚህች የተወለደ እንደምን ያደርገን ይሆን ብለው በጠላትነት ተነሱባቸው፤ መልአክ ኢያቄምን አድባረ ሊባኖስ ይዘሃት ሂድ ብሎት አድባረ ሊባኖስ ሄዳ ወልዳታለች፡ እም ሊባኖስ ትወፅእ መርዓት ያሰኘው ቅሉ ይህ ነው፡፡ ኦ ድንግል አኮ በተላህዮ ዘልሕቂ ከመ ዐዋልደ ዕብራውያን እለያገዝፉ ክሣዶን፡፡ አላ በቅድስና ወበንጽሕ ውስተ ቤተመቅደስ ነበርኪ፡፡ ይቆየን ! (ቅዳሴ ማርያም)
 “እምሊባኖስ ትወፅእ መርዓት … ሙሽራ /እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም/ ከሊባኖስ ትወጣለች” በማለት ጠቢቡ የተናገረው ቃለ ትንቢት ነው፡፡ /መኃ.4፥8/ 
ፈጣሪያችን ልዑል እግዚአብሔር ለተዋሕዶ ከመረጣት ከዓለመ አንስት ተለይታ በንጽሕና በቅድስና አጊጣ የመመኪያችን ዘውድ ከሆነች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በረከት ረድኤት ይክፈለን፡፡
 ምንጭ ደቂቀ ናቡቴ ወስብህት ወለአለም አለም አሜን፡፡

ሰማእት መጥምቀ መለኮት ዮሐንስ



በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን
  “የመጥምቁን የዮሐንስን ራስ በዚህ በወጭት ስጠኝ!!!!” ማቴ. ፲፬፡፰ /14፡8/
  በዚህ ዕለት “የቅዱሳኑ ሞት በእግዚአብሔር ፊት የከበረ ነው።” መዝ.115/116፡15 እንዲል ወንጌል መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ አንገቱ የተሰየፈበት ዕለት መታሰቢያ ክብረ በዓል ነው።
“እኔም ለዚህ ነገር አዋጅ ነጋሪና ሐዋርያ በእምነትና በእውነትም የአሕዛብ አስተማሪ ለመሆን ተሾምሁ፤ እውነት እናገራለሁ፤ አልዋሽም።” ፩ጢሞ.፪፡፯/1ጢሞ.2፡7/
  እንዲል ወንጌል ሐዋርያው ሰማዕት መጥመቀ መለኮት ቅዱስ
ዮሐንስ ንጉሱን ሳይፈራ ከአምላኩ የሕይወትን አክሊል ከሰጪው እግዚአብሔር ሊቀበል እውነትን ሰበከ፤ እውነትን አስተማረ። እንዲህም ሲልም ጨኸ፤ “በዚያም ወራት መጥምቁ ዮሐንስ። መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስሐ ግቡ ብሎ በይሁዳ ምድረ በዳ እየሰበከ መጣ። በነቢዩ በኢሳይያስ። የጌታን መንገድ አዘጋጁ ጥርጊያውንም አቅኑ እያለ በምድረ በዳ የሚጮህ ሰው ድምፅ የተባለለት ይህ ነውና ራሱም ዮሐንስ የግመል ጠጉር ልብስ ነበረው፥ በወገቡም ጠፍር ይታጠቅ ነበር፤ ምግቡም አንበጣና የበረሀ ማር ነበረ።” ማቴ.፫፡፩-፬ /ማቴ.3፡1-4/ /ማር.፩፡፩-፮ /ማር.1፡1-6/ ዮሐ.፩፡፳፫ /1፡23/
“ነቢዩ ኢሳይያስ እንዳለ። የጌታን መንገድ አቅኑ ብሎ በምድረ በዳ የሚጮኽ ሰው ድምፅ እኔ ነኝ አለ።” ዮሐ.፩፡፳፫ /1፡23/
  ሄሮድስ የወንድሙን የፊልጶስን ሚስት ሄሮድያዳን አግብቶ ነበርና በእርስዋ ምክንያት ራሱ ልኮ ዮሐንስን አስይዞ በወኅኒ አሳስሮት ነበር፤ ዮሐንስ ሄሮድስን። የወንድምህ ሚስት ለአንተ ልትሆን አልተፈቀደም ይለው ነበርና። ሄሮድያዳ ግን ተቃውማው ልትገድለው ትፈልግ ነበር አልቻለችም፤ ሄሮድስ ዮሐንስ ጻድቅና ቅዱስ ሰው እንደ ሆነ አውቆ ይፈራውና ይጠባበቀው ነበር፤ እርሱንም ሰምቶ በብዙ ነገር ያመነታ ነበር፤ በደስታም ይሰማው ነበር። ሄሮድስም በተወለደበት ቀን ለመኳንንቱና ለሻለቆቹ ለገሊላም ሹማምንት ግብር ባደረገ ጊዜ ምቹ ቀን ሆነላትና የሄሮድያዳ ልጅ ገብታ ስትዘፍን ሄሮድስንና ከእርሱ ጋር የተቀመጡትን ደስ አሰኘቻቸው። ንጉሡም ብላቴናይቱን። የምትወጂውን ሁሉ ለምኚኝ እሰጥሽማለሁ አላት፤ የመንግሥቴ እኩሌታ ስንኳ ቢሆን የምትለምኚውን ሁሉ እሰጥሻለሁ ብሎ ማለላት። ወጥታም ለእናትዋ። ምን ልለምነው? አለች። እርስዋም። የመጥምቁን የዮሐንስን ራስ አለች። ወዲያውም ፈጥና ወደ ንጉሡ ገብታ። የመጥምቁን የዮሐንስን ራስ በወጭት አሁን ልትሰጠኝ እወዳለሁ ብላ ለመነችው። ንጉሡም እጅግ አዝኖ ስለ መሐላው ከእርሱም ጋር ስለ ተቀመጡት ሊነሣት አልወደደም። ወዲያውም ንጉሡ ባለ ወግ ልኮ ራሱን እንዲያመጣ አዘዘው። ሄዶም በወኅኒ ራሱን ቈረጠ፥ ራሱንም በወጭት አምጥቶ ለብላቴናይቱ ሰጣት፥ ብላቴናይቱም ለእናትዋ ሰጠች። ደቀ መዛሙርቱም ሰምተው መጡ በድኑንም ወስደው ቀበሩት። ማር.፮፤፲፯-፳፱ /6፡17-29/ ማቴ.፲፬፡፩-፲፫ /ማቴ.14፡1-13/
  “ልትቀበለው ያለህን መከራ አትፍራ። እነሆ፥ እንድትፈተኑ ዲያብሎስ ከእናንተ አንዳንዶቻችሁን በወኅኒ ሊያገባችሁ አለው፥ አሥር ቀንም መከራን ትቀበላላችሁ። እስከሞት ድረስ የታመንህ ሁን የሕይወትንም አክሊል እሰጥሃለሁ።” ራዕይ ፪፡፲ /2፡10/ እንዲል ወንጌል አንገቱ ለ15 ዓመታት ክንፍ አውጥታ አስተምራ ሚያዝያ 15 አርፋለች። ክብሩ እንደምን ነው ቢሉ ጌታውን ለማጥመቅ በመብቃቱ ጌታም #አማን እብለክሙ ኢተንስአ እምትውልደ አንስት ዘየዐብዩ ለዮሐንስ# ትርጉሙም “እውነት እላችኋለሁ ከሴቶች ከተወለዱት መካከል ከመጥምቁ ዮሐንስ የሚበልጥ አልተነሳም” ማለት ነው። (ማቴ.11፡11) ብሎ ጌታ መስክሮለታል። በተስፋ ያመነው በቃልኪዳኑ የተማጸነውን እስከ ፶ (50) ትውልድ ሊምርለት ጌታ ቃል ኪዳን ገብቶለታል።
"ኪዳንየ ተካየድኩ ምስለ ሕሩያንየ"  (መዝ.88/89፡3) 
  “ከመረጥሁት ጋር ቃል ኪዳኔን አደረግሁ” ሲነቅፉአችሁና ሲያሳድዱአችሁ በእኔም ምክንያት ክፉውን ሁሉ በውሸት ሲናገሩባችሁ ብፁዓን ናችሁ። ዋጋችሁ በሰማያት ታላቅ ነውና ደስ ይበላችሁ፥ ሐሴትም አድርጉ፤ ከእናንተ በፊት የነበሩትን ነቢያትን እንዲሁ አሳድደዋቸዋልና። ማቴ.፭፡፲፩-፲፪/5፡11-12/ ከቅዱስ ዮሐንስ ረድኤትና በረከቱን ይክፈለን አሜን።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር ለዘበቅዱሳኒሁ ይሴባሕ ይእዜኒ ወዘልፈኒ ወለዓለም ዓለም አሜን፡፡ ወአሜን ለይኩን ለይኩን፡፡

ስላሴ



                      በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን::
ሥላሴ የሚለው ሠለሰ ሦስት አደረገ ከሚለው የግዕዝ ስርወ ቃል የተገኘ ሲሆን ሶስት ሦስትነት ማለት ሲሆን በያዘው ምስጢር ግን አንድም ሦስትም ተብሎ ይተረጎማል፡፡ ሦስትነታቸው በስም በአካል በግብር አንድነታቸው በባሕሪይ በሕልውና በመለኮት በሥልጣን በፈቃድ ነው፡፡
፩. የስም ሦስትነት፡- አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ተብሎ ነው፡፡ ማቴ28፡19
፪. የአካል ሦስትነት፡- ለአብ
ፍጹም አካል ፍጹም ገጽ ለወልድ ፍጹም አካል ፍጹም ገጽ ለመንፈስ ቅዱስ ፍጹም አካል ፍጹም ገጽ አለው መዝ 33፡15 መዝ118፡ 73 ኢሳ 66፡1 ዘፍ 18፡1-4 ማቴ 3፡16
፫. የግብር ሶስትነት፡- የአብ ግብሩ መውለድ ማሥረጽ የወልድ ግብሩ መወለድ የመንፈስ ቅዱስ ግብሩ መሥረጽ ነው፡፡ አብ ወላዲ ወልድ ተወላዲ መንፈስ ቅዱስ ሰራጺም ስላልን የሚበላለጡ አይደሉም አንድ ናቸው እንጂ፡፡ ዮሐ 10፡30 ምስጋና ይገባል አንድም ሦስትም ለሆኑ ለቅድስት ሥላሴ።
ለህታዌክሙ፡- አብ፡ወልድ፡መንፈስ፡ቅዱስ፡ሆይ፡ የፍጥረት ሁሉ ስነ ባህርይ ፈጥሮ በበላይነት ለሚገዛ መለኮታዊ ሥነ አእምሮ ሰላምታ ይገባል፡፡
ሥሉስ ቅዱስ ሆይ፡- በተመኘሁ ጊዜ የክብር ሦስትነታችሁን ለማግኘት ተመራምሮ አንድነትን ከሦስትነት ሳይቀላቅል የመለኮት አንድነት በዘላለማዊት ሕልውና አምናለሁ፡፡
ለዝክረ ስመክሙ፡- አብ፡ወልድ፡መንፈስ፡ቅዱስ፡ሆይ፡- ከሦስትነት ዝቅ ወይም ከፍ ለማይል የስም አጠራራችሁ ሰላምታ ይገባል፡፡
ሥሉስ ቅዱስ ሆይ፡- በሦስትነት ጸንቶ ለሚኖር የባህርይ አምላክነታችሁ መለኮታዊ እጅ ከተከለው፡ ተክለ ጽድቅ ፍሬያችሁከወይን ዘለላ ቸርነታችሁ ትመግቡኝ ዘንድ ደጅ እጠናለሁ እኔ አገልጋያችሁ (ከመልከአ ሥላሴ የተወሰደ)

የዓለም ገዢ ሥሉስ ቅዱስ ሆይ፡-
በወዳጃችሁ በአርሃም እንደገባችሁ ከእናንተ ዘንድ የሚሰጠውን ሰማዕትነት በአክሊል እቀዳጅ ዘንድ ተድላ ደስታ ካለበት ገነት አግቡኝ፡፡ ሃጢአቴን በይቅርታ ቃል ደምስሳችሁነፍሴን ከሚቃወሟት አጋንንት አድኗት፡፡
አብ፡ወልድ፡መንፈስ፡ቅዱስ፡ሆይ፡- በእውነት ስማችሁን እጠራ ዘንድ ከወደኩበት አንሱኝ ከሩቅ ጥቀሱኝ ከቀትር ጋኔን ከድንገተኛ መጋኛ ትጠብቁኝ ዘንድ እማጸናለሁ፡፡
አብ፡ወልድ፡መንፈስ፡ቅዱስ፡ሆይ፡-የምስጋና፡ፍሬ፡እንዳፈራና፤ከአንደበቴም፡የጸሎት፡እሸት፡አበረክትላችሁ፡ዘንድ፡በልቡናዬ፡እርሻ፡ላይ፡መልካሙን፡ፍሬ፡ትዘሩ፡ዘንድ፡እማፀናለው፡፡ (ሰይፈ ሥላሴ ዘዘወትር)

“ወንድሞቻችን እኛስ እንዲህ እናምናለን ያልተወለደ እግዚአብሔር አብ በተለየ አካሉ አንድ ነው፤የተወለደ እግዚአብሔር ወልድ ዋሕድ ኢየሱስ ክርስቶስም በተለየ አካሉ አንድ ነው፡፡ በወደደው የሚያድር የአብ የወልድ እስትንፋስ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስም በተለየ አካሉ አንድ ነው፡፡አብ አልተወለደም ዓለም ሁሉ ሳይፈጠር ወልድን የወለደ ነው እንጂ ወልድም ዓለም ሁሉ ሳይፈጠር ከእግዚአብሔር አብ ተወለደ፤መንፈስ ቅዱስም ዓለም ሁሉ ሳይፈጠር ከእግዚአብሔር አብ ሠረጸ፡፡ (ሃይማኖተ አበው ዘአትናቲዎስ ገጽ ፶፭፡፡)
“ሰናቋርጥ የሦስቱን ምስጋና አንድነት እንናገራለን ፍጹም አሸናፊ አንድ አምላክ እግዚአብሔር አብ፤ወልድ መንፈስ ቅዱስ ሆይ ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ ተብለህ የምትመሰገነው ምስጋናህ በሰማይ በምድር ምሉ ነው፡፡ ( ሃይማኖተ አበው ዘጎርጎርዮስ ገጽ ፩፻፲፪ ፡፡)
“አብ በአካሉ በገጹ በመልኩ ያለ ነውና ወልድም እንዲሁ በአካሉ በገጹ በመልኩ ያለ ነውና መንፈስ ቅዱስም እንዲሁ በአካሉ በገጹ በመልኩ ያለ ነውና እንደሰውም አይወሰኑም አምላክነት ያለው አካላት ናቸውና፡፡ በአካል ሦስት በባሕርይ አንድ ብሎ ይህን ሃይማኖት የማያምን አንዲህ እኛ እንደወሰንነው አድርጎ ሃይማኖቱን የማይጽፍ ቢኖር ሐዋርያት ያስተማሯት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ታወግዘዋለች” ( ሃይማኖተ አበው ዘአትናቴዎስ ገጽ ፹፩ ፦ም.፳፮ ፡፡)


በቀትርም ጊዜ እርሱ በድንኳኑ ደጃፍ ተቀምጦ ሳለ እግዚአብሔር በመምሬ የአድባር ዛፍ ተገለጠለት። ዓይኑንም አነሣና እነሆ፥ ሦስት ሰዎች በፊቱ ቆመው አየ፤ ባያቸውም ጊዜ ሊቀበላቸው ከድንኳኑ ደጃፍ ተነሥቶ ሮጠ፥ ወደ ምድርም ሰገደ፥ እንዲህም አለ። አቤቱ፥ በፊትህስ ሞገስ አግኝቼ እንደ ሆነ ባሪያህን አትለፈኝ ብዬ እለምናለሁ፤ ጥቂት ውኃ ይምጣላችሁ፥ እግራችሁን ታጠቡ፥ ከዚህችም ዛፍ በታች ዕረፉ፤ቍራሽ እንጀራም ላምጣላችሁ፥ ልባችሁንም ደግፋ ከዚያም በኋላ ትሄዳላችሁ፤ ስለዚህ ወደ ባሪያችሁ መጥታችኋልና። እነርሱም። እንዳልህ አድርግ አሉት። አብርሃምም ወደ ድንኳን ወደ ሣራ ዘንድ ፈጥኖ ገባና። ሦስት መስፈሪያ የተሰለቀ ዱቄት ፈጥነሽ አዘጋጂ፥ ለውሺውም፥ እንጎቻም አድርጊ አላት። አብርሃምም ወደ ላሞቹ ሮጠ፥ እጅግ የሰባም ታናሽ ጥጃ ያዘና ለብላቴናው ሰጠው፥ ያዘጋጅም ዘንድ ተቻኰለ። እርጎና ወተትም ያዘጋጀውንም ጥጃ አመጣ፥ በፊታቸውም አቀረበው፤ እርሱም ከዛፉ በታች በፊታቸው ቆሞ ነበር፥ እነርሱም በሉ። እነርሱም። ሚስትህ ሣራ ወዴት ናት? አሉት። እርሱም። በድንኳኑ ውስጥ ናት አላቸው።
እርሱም። የዛሬ ዓመት እንደ ዛሬው ጊዜ ወደ አንተ በእውነት እመለሳለሁ፤ ሚስትህ ሣራም ልጅን ታገኛለች አለ። ሣራም በድንኳን ደጃፍ በስተ ኋላው ሳለች ይህንን ሰማች። አብርሃምና ሣራም በዕድሜአቸው ሸምግለው ፈጽመው አርጅተው ነበር፤ በሴቶች የሚሆነውም ልማድ ከሣራ ተቋርጦ ነበር። ሣራም በልብዋ እንዲህ ስትል ሳቀች። ካረጀሁ በኋላ በውኑ ፍትወት ይሆንልኛልን? ጌታዬም ፈጽሞ ሸምግሎአል። እግዚአብሔርም አብርሃምን አለው። ካረጀሁ በኋላ በውኑ እወልዳለሁን? ስትል ሣራ ለምን ሳቀች? በውኑ ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር አለን? የዛሬ ዓመት እንደ ዛሬው ጊዜ ወደ አንተ እመለሳለሁ፤ ሣራም ልጅን ታገኛለች። ሣራም ስለ ፈራች። አልሳቅሁም ስትል ካደች። እርሱም። አይደለም፥ ሳቅሽ እንጂ አላት። ሰዎቹም ከዚያ ተነሥተው ወደ ሰዶም አቀኑ፤ አብርሃምም ሊሸኛቸው አብሮአቸው ሄደ። እግዚአብሔርም አለ። እኔ የማደርገውን ከአብርሃም እሰውራለሁን? አብርሃም በእውነት ታላቅና ብርቱ ሕዝብ ይሆናልና፥ የምድር አሕዛብም ሁሉ በእርሱ ይባረካሉና። ጽድቅንና ፍርድን በማድረግ የእግዚአብሔርን መንገድ ይጠብቁ ዘንድ ልጆቹንና ከእርሱ በኋላ ቤቱን እንዲያዝዝ አውቃለሁና፤ ይህም እግዚአብሔር በአብርሃም ላይ የተናገረውን ነገር ሁሉ ያመጣ ዘንድ ነው። እግዚአብሔርም አለ። የሰዶምና የገሞራ ጩኸት እጅግ በዝቶአልና፥ ኃጢአታቸውም እጅግ ከብዳለችና፥ እንግዲህስ ወደ እኔ እንደ መጣች እንደ ጩኸትዋ አድርገው እንደ ሆነ ወርጄ አያለሁ፤ እንዲሁም ባይሆን አውቃለሁ። ሰዎቹም ከዚያ ፊታቸውን አቀኑ፥ ወደ ሰዶምም ሄዱ፤ አብርሃም ግን በእግዚአብሔር ፊት ገና ቆሞ ነበር። አብርሃምም ቀረበ አለም። በውኑ ጻድቁን ከኃጢአተኛ ጋር ታጠፋለህን? አምሳ ጻድቃን በከተማይቱ ውስጥ ቢገኙ በውኑ ሁሉን ታጠፋለህን? ከተማይቱንስ በእርስዋ ስለሚገኙ አምሳ ጻድቃን አትምርምን? ይህ ከአንተ ይራቅ፤ ጻድቁን ከኃጢአተኛ ጋር ትገድል ዘንድ፥ ጻድቁም እንደ ኃጢአተኛ ይሆን ዘንድ፥ እንደዚህ ያለው አድራጎት ከአንተ ይራቅ። የምድር ሁሉ ፈራጅ በቅን ፍርድ አይፈርድምን? እግዚአብሔርም። በሰዶም በከተማይቱ ውስጥ አምሳ ጻድቃን ባገኝ ስፍራውን ሁሉ ስለ እነርሱ እምራለሁ አለ። አብርሃምም መለሰ አለም። እኔ አፈርና አመድ ስሆን ከጌታዬ ጋር እናገር ዘንድ እነሆ አንድ ጊዜ ጀመርሁ፤ ከአምሳው ጻድቃን አምስት ቢጐድሉ ከተማይቱን ሁሉ በአምስቱ ምክንያት ታጠፋለህን? ከዚያ አርባ አምስት ባገኝ አላጠፋትም አለ። ደግሞም ተናገረው፥ እንዲህም አለ። ምናልባት ከዚያ አርባ ቢገኙሳ? እርሱም። ለአርባው ስል አላደርገውም አለ። እርሱም። ጌታዬ አይቆጣ እኔም እናገራለሁ ምናልባት ከዚያ ሠላሳ ቢገኙሳ? አለ። እርሱም ከዚያ ሰላሳ ባገኝ አላጠፋም አለ። ደግሞም። እነሆ፥ ከጌታዬ ጋር እናገር ዘንድ አንድ ጊዜ ጀመርሁ፤ ምናልባት ከዚያ ሀያ ቢገኙሳ? አለ። እርሱም። ከዚያ ሀያ ቢገኙ ስለ ሀያው አላደርገውም አለ። እርሱም። እኔ ደግሞ አንድ ጊዜ ብቻ ብናገር ጌታዬ አይቆጣ፤ ምናልባት ከዚያ አሥር ቢገኙሳ? አለ። እርሱም። ስለ አሥሩ አላጠፋትም አለ። እግዚአብሔርም ከአብርሃም ጋር ንግግሩን በጨረሰ ጊዜ ሄደ፤ አብርሃምም ወደ ስፍራው ተመለሰ። (ዘፍ.፲፰፡፩-፴፫) 18፡1¬-33
ካለመኖር ወደ መኖር ያመጣኝ፣ ካለማወቅ ወደ መረዳት ያደረሰኝ አነሳስቶ ላስጀመረኝ አስጀምሮ ላስፈጸመኝ ጥንት ላሌለው ቀዳማዊ ፍጻሜ ላሌለው ድህራዊ ያልኖረበት ጊዜ የሌለ የማይኖርበት ጊዜም የማይኖር የዘላለም ንጉስ ሁሉን ቻይ ፈጣሪ እግዚአብሔርን በራስ ፀጉሬ ቁትር በአጥንቶቼም ልክ አመሰግናለሁ፡፡
በሰማይ ያሉ መላእክት በምድርም የሚኖሩ የአዳም ዘር ሁሉ የሚያመሰግኗት በአማላጅነቷ ሁል ጊዜ የማትለየኝ ከፀሐይ ሰባት እጅ የምታበራ የብርሃን እናት የሁሉ እመቤት የአምላክ እናት ከተመረጡ የተመረጠች ከተለዩ የተለየች ከተከበሩ የተከበረች እናቴ እመቤቴ ድንግል ማርያም በቃላት ልገልጸው ከምችለው በላይ አመሰግናለሁ፡፡ ሌሊትና ቀን ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ እያሉ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔርን የሚያመሰግኑና ሳይሰለቹ የሚጠብቁን ሊቀነ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ቅዱስ ገብርኤል ቅዱስ ሩፋኤል ቅዱስ ዑራኤል ቅዱስ ራጉኤል ቅዱስ ፋኑኤል እልፍ አእላፋት የሆኑ ጠባቂ መላእክት ሳመሰግን በደስታ ነው፡፡
በጸሎታቸው ያልተለዩኝን ጻድቃን አባቶቼን አቡነ ተክለሃይማኖትን አቡነ ገብረምንፈስ ቅዱስን አቡነ ሀብተማርያምን አቡነ አረጋዊን አቡነ ኪሮስንና ሌሎች ቅዱሳን አባቶቼን እንዲሁም እናቶቼን ቅድስት ክርስቶስ ሰምራን ቅድስት አርሴማን ብዙ ያልጠቀስኳቸው ቅዱሳንን ለማመስገን ቃላት የለኝም፡፡
በሰማዕትነታቸው የጥንካሬ ምሳሌ የሆኑልኝ በጸሎታቸው የረዱኝን ቅዱሳን ሰማዕታት ቅዱስ ጊዮርጊስን ቅዱስ እስጢፋኖን መጥመቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስንና ሌሎችን ቅዱሳን ሰማዕታትን ሁሉ በእጅጉ አመሰግናለሁ ለዘላለሙ አሜን፡፡
የእግዚአብሔር፣ቸርነት የድንግል ማርያም አማላጅነት፣ የቅዱሳን መላእክት ተራዳኢነት፣ የጻድቃን፣ የሰማዕታት፣ የቅዱሳን ሐዋርያት፣ የቅዱሳን አበው መነኮሳት፣ የቅዱሳት አንስት፣ የደናግላንና የቅዱሳን ሁሉ ምልጃና ቃል-ኪዳናቸው ባለንበት ከሁላችን ጋር ይሁን ይቆየን፡፡
  ወስብሐት ለእግዚአብሔር ለዘበቅዱሳኒሁ ይሴባሕ ይእዜኒ ወዘልፈኒ ወለዓለም ዓለም አሜን፡፡ ወአሜን ለይኩን ለይኩን፡፡

ፃድቁ አባታችን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ



      “እግዚአብሔር ያፈቅሮሙ ለጻድቃን እግዚአብሔር የዐቅቦሙ ለፈላስያን፡፡“ (እግዚአብሔር ጻድቃንን ይወድዳል፤ እግዚአብሔር ስደተኞችን ይጠብቃል፡፡)“ መዝ.፻፵፭፡፰ (145፡8)

                                        በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ
ዝክረ ጻድቅ ለዓለም ይሄሉ (የጸድቅ መታሰቢያ ለዘላለም ይኖራል።)†heart† መዝ.111፡6
ቅድመ ዓለም ዘሀሎ አለም ከመፈጠሩ በፊት ለነበረ ለእግዚአብሔር አብ እና የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ሥጋን ለለበሰ ለእግዚአብሔር ወልድ እንዲሁም ከእነሱ ባለመራቅ ለሚኖር ለእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስም ምስጋና ይገባል፡፡ ስለ ጻድቁ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ በማብዛት አይደለም በማሳነስ በማስረዘም አይደለም በማሳጠር እንድጽፍ ያነሳሳኝ እግዚአብሔር ክብርና ምስጋና ጌትነትና ውዳሴ ይገባዋል አሜን በእውነት፡፡

  “እግዚአብሔር ያፈቅሮሙ ለጻድቃን እግዚአብሔር የዐቅቦሙ ለፈላስያን፡፡“ (እግዚአብሔር ጻድቃንን ይወድዳል፤ እግዚአብሔር ስደተኞችን ይጠብቃል፡፡)“” መዝ.፻፵፭፡፰ (145፡8)
  አባታችን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ሀጋራቸው ንሂሳ ግብጽ ነው፡፡ አባታቸው ስምዖን እናታቸው አቅሌስያ፡ ይባላሉ፡፡ ልጅ አጥተው 30 ዘመን ሲያዝኑ ኖረዋል፡፡ አንድ ቀን አቅሌሲያ ቤተ እግዚአብሔር ገብታ ከሥዕለ ሥላሴ ሥር ወድቃ ስትማጸን ክብሩ ከሰማይ ከፍታ የሚበጥ ልጅ እንኪ ተቀበይ የሚል ድምጽ ሰማች፡፡ በዚሁ መሰረት አባታችን መጋቢት 29 ተጸንሰው ታህሳስ 29 ተወለዱ፡፡ ዓይን በገለጹ ጊዜ ከሚታይ ነገር ላይ እንዲያርፍ እርሳቸውም በተወለዱ ጊዜ አፈፍ ተነስተው “ስብሐት ለአብ ስብሐት ለወልድ ስብሐት ለመንፈስ ቅዱስ ዘአውጻእከኒ እምጽ ልመት ውስተ ብረሃን” ብለው በማመስገናቸው ኋላም ምድራዊ መብል መጠጥ ሳይመገቡ ሳይጠጡ ለምስጋና ተግተው በመኖራቸው መላዕክትን ይመስላሉ፡፡
  ሦስት ዓመት ሲሆናቸው ቅዱስ ገብርኤል ከእመቤታችንና በገነት ካሉ ቅዱሳን ዘንድ አስባርኮ ገዳማውያን ካሉበት ምኔት ወስዶ ከበሩ አኖራቸው፡፡ አባ ዘመደ ብርሃን አሳድጎ አስተምሮ ከመዓርገ ምንኩስና አድርሷቸዋል፡፡ ከዚህ በኋላ “ሀብተ ፈውስ” ተሰቷቸዋል፡፡ በአንድ ቀን እልፍ እውራንንና አንካሳን ፈውሷል፡፡ ኋላ ግን ኤጲስ ቆጶሳቱ ካህናቱ ዝናቸውን ሰምተው እየመቱ ግብር የሚያስፈቷቸው ቢሆን ቅዱስ ገብርኤል በክንፉ ነጥቆ ከጌታ ፊት አቀረባቸው፡፡ በገድልህ በትሩፋትህ ከሞተ ነፍስ ከርደተ ገሃነም የሚድኑ ብዙ ነፍሳት አሉና ከሰው ተለይተህ ወደ ጫካ ግባ፡፡ ኑሮህም ከ60 አናብስተና ከ60 አናምርት ጋር ይሁን አላቸው፡፡ ጌታዬ ምን ተመግበው ይኖራሉ? ብለው ጌታን ጠየቁት፡፡ “ዘኬድከ ጸበለ-እገሪከ ይልህሱ ወበውእቱ ይጸግቡ…” የረገጥከውን ትቢያ ልሰው ያው ምግብ ሆኗቸው ይኖራሉ፡፡ ብሏቸው ውሳጤ ገዳም ገብተው ከአናብስትና አናምርት ጋር ይኖሩ ጀመር፡፡ ዳንኤል በአናብስት ጉድጓድ በጣለ ጊዜ አናብርቱ እንደ ድመት ከእግሩ በታች ሆነው እንደተገኙ የረገጡትን ትቢያ ይልሱ ይታዘዟቸውም ነበር፡፡ በዚህ መልኩ መልአኩ 30 ዓመት ከቆዩ በኋላ ጌታ ባንድነት በሦስትነት ተገልጾ “ምን ላድርግልህ ትሻለህ?” አላቸው፡፡ መጀመሪያ ላሉበት መጸለይ ይገባልና የምድረ ጋቦታን ሰዎች ማርልኝ አሉት፡፡ 3000 ሃጥአንን ከሲኦል አውጥቶ ገነት አግብቶላቸዋል፡፡ “ሑር ምድረ ኢትዮጵያ ወበህየኒ ሀላውከ ነፍሳት ዘታወጽኦሙ ወደ ኢትዮጵያ ሂድ” አላቸው፡፡ ቅዱስ ገብርኤል በሰረገላ ነፋስ ጭኖ ምድረ ከብድ አድርሷቸዋል፡፡ ዳግመኛም ወደ ዝቋላ ደብር ቅዱስ ወስዷቸው ከዚያ ሆነው በንጽሐ ልቦና የኢትዮጵያን ሕዝብ ሃጢአት አይተው ከባሕሩ በራሳቸው ቆመው ይጸልዩ ጀመር፡፡ አርባ ቀን ሲሆናቸው መልአኩ መጥቶ “ዘገብረ ተዝካረከ ወዘጸውዐ ስመከእምሕር ለከ ብሎሀል” አላቸው፡፡ መላ ኢትዮጵያን ካልማረልኝ አልወጣም ብለው መቶ አመት ሲጸልዩ ኑረዋል፡፡ ከመቶ አመት በዃላ ጌታ “ተንስእ ወጻእ መሐርኩ ለከ ኩሎ ኢትዮጵያ ምሬለሃለሁ ውጣ” ብሏቸው ወጥተዋል፡፡
  ከዚህ በኋላ ምድረ ከብድ ወርደው ከምድር በላይ ከሰማይ በታች ሆነው ሰባት ዓመት እንደ ትኩል አምድ ሆነው ዓይናቸውን ሳይከድኑ ሰባት ዓመት ቆመው ጸልየዋል፡፡ ሰይጣንም በምቀኝነት ተነሳስቶ ቁራን መስሎ መጥቶ አይናቸውን አንቁሮ አሳወራቸው፡፡ ሁለት ሱባኤ ሲፈጽሙ ቅዱስ ሚካኤልና ቅዱስ ገብርኤል መጥተው እፍ ብሏቸው አድነዋቸዋል፡፡ ከዚያ ተነስተው ወደ ዝቋላ ሲሄዱ ሥላሴን በአምሳለ አረጋውያን ከጥላ ስር አርፈው አገኟቸው፡፡ በእግዚአብሔር ዙፋን ተማጽነናል አዝለህ አንድ አንድ ምዕራፍ ሸኘን አሏቸው፡፡ አዝለው ከሸኙአቸው በኋላ በአንድነት በሦስትነት ሆኖ ታያቸው ደንግጠው ወደቁ፡፡ አንስተው ዝቋላ ወርደህ ጠላቶችህን ተበቀላቸው አሏቸው፡፡በዘባነ መብረቅ ደርሰው ሰባቱን ሊቃነ መላእክት አጋዥ አርድገው እልፍ አዕላፍ አጋንንትን በማጭድ አጭደዋል፡፡ እንዲህ ለሰሚዕ እፁብ በሆነ ግብር ዓመት በኢትዮጵያ 262 ኖረው በ562 ዓመታቸው በተስፋቸው ያመነውን በኪዳናቸው የተማጸነ ጌታ ከመከራ ሥጋ ከመከራ ነፍስ ሊምርላቸው ተስፋቸውን ተቀብለው  በዕለት በዕለተ እሁድ ዐርፈዋል፡፡
  መላእክት በአክናፈ እሳት ኢየሩሳሌም ወስደው በየማነ ምስዋዕ ቀብረዋቸዋል፡፡
ሮሜ 12፡12፣ 15፡30፣ያዕ5፡16፣ መዝ.88፡3፣111፡6 ምሳ.10፡7 ማቴ10፡40-42
  ወደ ኢትዮጵያ የመጡት በቅዱስ ላሊበላ ዘመነ መንግስት መሆኑ ስለሚታወቅ ከ9- 14ኛው ም/ዓ ድ/ል/ክ መሆኑ ነው፡፡
  ካለመኖር ወደ መኖር ያመጣኝ፣ ካለማወቅ ወደ መረዳት ያደረሰኝ አነሳስቶ ላስጀመረኝ አስጀምሮ ላስፈጸመኝ ጥንት ላሌለው ቀዳማዊ ፍጻሜ ላሌለው ድህራዊ ያልኖረበት ጊዜ የሌለ የማይኖርበት ጊዜም የማይኖር የዘላለም ንጉስ ሁሉን ቻይ ፈጣሪ እግዚአብሔርን በራስ ፀጉሬ ቁትር በአጥንቶቼም ልክ አመሰግናለሁ፡፡
  በሰማይ ያሉ መላእክት በምድርም የሚኖሩ የአዳም ዘር ሁሉ የሚያመሰግኗት በአማላጅነቷ ሁል ጊዜ የማትለየኝ ከፀሐይ ሰባት እጅ የምታበራ የብርሃን እናት የሁሉ እመቤት የአምላክ እናት ከተመረጡ የተመረጠች ከተለዩ የተለየች ከተከበሩ የተከበረች እናቴ እመቤቴ ድንግል ማርያም በቃላት ልገልጸው ከምችለው በላይ አመሰግናለሁ፡፡
ምንጭ፡- መዝገበ ታሪክ፣ ነገረ ቅዱሳን፣ የወርሃ ጥቅምት ስንክ ሳርና ገድላቸው፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር ለዘበቅዱሳኒሁ ይሴባሕ ይእዜኒ ወዘልፈኒ ወለዓለም ዓለም አሜን፡፡ ወአሜን ለይኩን ለይኩን፡፡