Thursday, November 28, 2013

ትምህርተ ጦም በሊቃውንት





በዚህ ጽሑፍ ጦምን አስመልክቶ የቅዱሳን አባቶችን አስተምህሮ እንመለከታለን
 
አንድ የገዳም አበምኔት  አንድ ወቅት አባ ጳይመን የሚባሉትን አባት “እግዚአብሔርን መፍራት እንዴት ገንዘቤ ማድረግ ይቻለኛል” ብለው  ይጠይቋቸዋል፡፡ እሳቸውም ሲመልሱ “እንዴት ሰው በላመና በጣፈጠ መብልና መጠጥ ሆዱን እየሞላ እግዚአብሔርን መፍራት ገንዘቡ ሊያደርግ ይችላል? ስለዚህም ጦም እግዚአብሔርን ወደመፍራት ይመራል፡፡ የጦም የመጨረሻ ግቡ እግዚአብሔርን ወደመፍራት ማምጣት  ነው”  ብለው ይመልሱላቸዋል፡፡
 
አንድ ወቅት አንድ ጠዋሚ በጦም ወቅት ማልዶ ይርበዋል፡፡ እናም ከሦስት ሰዓት በፊት ላለመመገብ ከፍላጎቱ ጋር ይሟገታል፡፡ ሦስት ሰዓትም ሲሆን እንደምንም ብሎ እስከ ስድስት ሰዓት ሊቆይ ይወስናል፡፡ ስድስት ሰዓት ደርሶ ሊመገብ ማዕዱን በቆረሰ ጊዜ እንደገና ለራሱ እስከ ዘጠኝ ሰዓት ልቆይ ብሎ በመናገር ምግቡን ከመመገብ ይከለከላል፡፡ ዘጠኝ ሰዓት ላይ ጸሎቱን አድርሶ ሊመገብ ሲል ሰይጣን ልክ እንደጭስ ከሰውነቱ ሲወጣ ታየው ወዲያው ረሃቡ ጠፋ፡፡
 
እየጦምክ ነውን? ለተራበ አብላ ፣ለተጠማም አጠጣ፣ ሕመምተኞችን ጎብኝ፣ የታሰሩትን ጠይቅ፣ በመከራ ላሉት እራራላቸው፣ በጭንቀት ወድቀው የሚያለቅሱትን አጽናናቸው፣ ርኅሩኅ፣ ትሑት፣የዋህ፣ ሰላማዊ፣ አዛኝ፣ይቅር ባይ፣ እውነተኛ እና ታማኝ ሁን፡፡ እንዲህ ከሆንክ እግዚአብሔር ጦምህን ይቀበልልሃል፡፡ ስለንስሐም ብዙ የንስሐ ፍሬን ይሰጥሃል፡፡ ጦም ለነፍስ ምግብ ነው፡፡
 ቁጣ መቼም ቢሆን የሚመከር አይደለም፤በተለይ በጦም ሰዓት ከቁጣ መራቅ ተገቢ ነው፡፡ ትሕትናንና ፣የዋሃትን ገንዘብህ አድርግ፤ክፉ ፈቃዶችንና አሳቦችን ተቃወማቸው፤ ራስህን መርምር በየእለቱ ወይም በሳምንት ውስጥ ምን መልካም እንደሠራህ አእምሮህን ጠይቀው፡፡ እንዲሁም ምን ስሕተትን ፈጽመህ እንደነበርና ስሕተትሕን ደግመህ እንዳትፈጽም የመፍትሔህ እርምጃዎች ምን ሊሆኑ እንዲገባቸው አሰላስል፡፡ ጦምህ እንዲህ ሊሆን ይገባዋልና፡፡
ምግብ ሰውነትን እንደሚያሰባ እንዲሁ ጦም ነፍስን ከሥጋ አስተሳሰብ ተላቃ ወደ ላይ በመነጠቅ ሰማያዊ ነገሮችን ለመመርመርና ከምድራዊ ደስታ ይልቅ እጅግ ግሩም የሆነ ደስታን ለማግኘት ጥንካሬን ይሰጣታል፡፡
 አርባ ቀን ሙሉ ከምግብ ተከልክዬ ጦምኩ አትበለኝ፡፡ ይህንና ያንን አልበላሁም ወይንም ከአፌ አልገባም አትበለኝ፡፡ እኔ ይህንን ካንተ አልሻም፣ ነገር ግን ከቁጣ ርቀህ ታጋሽ መሆንህን አሳየኝ፤ ከጭካኔህ ተመልሰህ አዛኝ ወደመሆን እንደመጣህ አሳየኝ፡፡ ነገር ግን ቁጣ የሞላብህ ከሆነ ስለምን ሥጋህን በጦም በከንቱ ትጎስማታለህ ? ሰዎችን ሁሉ የምትጠላና ስስታም ከሆንክ ለአንተ ከምግብ ተከልክለህ ውሃ ብቻ መጠጣትህ ምን ትርፍ ያመጣልሃል?
ጦም እጅግ ግሩም የሆነ ነገር ነው፡፡ ኃጢአታችንን እንደማይጠቅም አረም ከውስጣችን ይነቅለዋል፡፡  እውነተኛው የጽድቅ ተክልም  በውስጣችን ልክ እንደ አበባ እንዲያብብ ይረዳዋል፡፡ (ቅዱስ ባሲልዮስ)
ጸሎት፣ ጦም ፣ትጋህ ሌሊት እና ሌሎችም አንድ ክርስቲያን የሚተገብራቸው ክርስቲያናዊ ተግባራት ምንም መልካሞች ቢሆኑ የክርስቲያናዊ ሕይወት ግቦች ግን አይደሉም፡፡ ነገር ግን ወደ ትክክለኛው ክርስቲያናዊ ሕይወት ለመድረስ የሚያገለግሉን መንፈሳዊ ትጥቆች ናቸው፡፡ትክክለኛው የክርስቲያን ግብ መንፈስ ቅዱስ በእርሱ ሰውነት ውስጥ ሥራ እንዲሠራ በመፍቀድ የመንፈስ ቅዱስ ፍሬዎችን አፍርቶ መገኘት ነው፡፡በዚህ ምድር የመንፈስ ቅዱስ ፍሬዎች ማፍራት እስካልቻልን ድረስ የእግዚአብሔርን መንግሥት መውረስ አይቻለንም፡፡ (ቅዱስ ሱራፊ)
የአዋጅ ጦም ሲገባ መንፈሳዊ የበጋ ወራቱ እንደገባ ልብ እንበል፡፡ ስለዚህም የጦር መሳሪያችንን እንወለውለው  ከእርሻቸው አዝመራውን የሚሰበሰቡትም ገበሬዎች ማጭዳቸውን ይሳሉ፤ ነጋዴዎችም በከንቱ ገንዘባቸውን ከማባከን ይከልከሉ፣ መንገደኞችም ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ለመግባት መንገዳቸውን ያቅኑ፡፡ ወደ እግዚአብሔር መንግሥት የምትወስደው ጎዳና ቀጭንና ጠባብ ናትና በጥንቃቄ እያስተዋላችሁ ተጓዙ፡፡
እንዲያው በልማድ ሰዎች እንደሚፈጽሙት ዓይነት ጦም ትጦሙ ዘንድ አልመክራችሁም፡፡ ነገር ግን ከምግብ ስለምንከለከልባት ጦም ብቻ ሳይሆን ከኃጢአት ስለምንከለከልባት  እውነተኛይቱ ስለሆነችው ጦም እጽፍላችኋለሁ፡፡ ጦም በባሕርይዋ በሕግ ካልተመራች  ለሚተገበሩዋት ሰዎች ዋጋን አታሰጥም፡፡ ስለዚህም ጦምን ለመጦም ስንዘጋጅ የጦም ዘውድ የሆነውን ነገር መዘንጋት የለብንም፡፡ ስለዚህ ስለምን ያ በእግዚአብሔር ቤተመቅደስ ደጅ ሆኖ ጸሎቱን ያደረሰው ፈሪሳዊ ከእግዚአብሔር ዘንድ ስለጦሙ አንዳች ዋጋ ሳያገኝ በባዶው እጁ እንደተመለሰ መረዳት ተቀዳሚ ተግባራችን ሊሆን ይገባዋል (ሉቃ. ፲፰፥፱-፲፬(18፡9-14))፡፡ ቀራጩ አልጦመም ነገር ግን ጸሎቱ ተሰምቶለታል፡፡ ጦም ሌሎች አባሪ የሚሆኑ መልካም ሥራዎች ካልታከሉበት በቀር ልክ እንደዚኛው ፈሪሳዊ ዋጋ አያሰጠንም፡፡
ጦም ማለት መድኃኒት ማለት ናት፡፡ እንደ ሌሎቹ መድኃኒቶች ሁሉ ጦምን እንዴት እንደሚጠቀምበት የሚያውቅ ሰው ዋጋ ያገኝበታል፡፡ በጥበብ ላልተጠቀመበት ሰው ግን የማይረባና የማይጠቅም ይሆንበታል፡፡ ከጦም የሚገኘው ክብር ከምግብ በመከልከላችን ምክንያት የምናገኘው ብቻ አይደለም፡፡ ከኃጢአት ሥራዎችም ፈጽመን በመከልከላችን ምክንያት የምናገኘው ክብር ጭምር ነው ፡፡ ጦም ሰይጣን ወደ እኛ እንዳይቀርብ እንደጋሻ የሚያገልግለን መሣሪያ ነው፡፡ ነገር ግን በጦም ሰዓት ኃጢአትን ፈቅደን የምንሠራት ከሆነ ሰይጣን አጥሩን ጥሶ እንዲገባና በእኛ ላይ እንዲሠለጥን ምክንያት እየሆንነው ነው፡፡ ጦማችን ከምግብ በመከልከል ብቻ የተወሰነ ከሆነ ጦምን እናስነቅፋታለን፡፡
እየጦምክ ነውን ? መጦምህን በሥራህ ገልጠህ አሳየኝ፡፡ ድሃው እርዳታህን ፈልጎ እንደሆነ ቸርነትን አድርግለት፡፡ ጠላት ያደረግኸውን ካየኸው ከእርሱ ጋር ፈጥነህ ታረቅ፡፡ ጓደኛህ ተሳክቶለት ካየኸው በእርሱ ላይ ቅናት አይደርብህ፡፡ አፍህ ብቻ አይጡም ዐይንህም ጆሮህም እግርህም እጅህም የሰውነትህ ሕዋሳቶች ሁሉ ክፉ ከማድረግ ይጡሙ፡፡
እጆችህ ከዝርፊያና ከሕግ ውጪ ለመክበር ሲባል ትርፍን ከማጋበስ ይጡሙ፡፡ እግሮችህ የኃጢአት ሥራን ለመፈፀም ከመፋጠን ይጡሙ፡፡ ዐይኖችህም ውጫዊ በሆነ ውበት ምክንያት ከመቅበዝበዝ ይጡሙ፡፡ የሚታዩ ነገሮች ለዐይን ምግቦች ናቸው፡፡ ነገር ግን ከእግዚአብሔር ሕግ ጋር የሚጣረሱ ምልከታዎች ጦምን ያፈርሳሉ፡፡ነፍስንም እንድትነዋወጥ ያደርጉአታል፡፡ የምናያቸውን ነገሮች ከእግዚአብሔር ሕግ ጋር የሚስማሙ ከሆኑ ጦማችንን ያስጌጡዋታል፡፡ በጦም ምክንያት በጦም ሰዓት መመገብ የተከለከሉትን ምግቦች መመገብ የሚያስነቅፍ ከሆነ ፤ እንዴት ታዲያ በዐይናችን እንድንመለከተው በሕግ የተከለከልነውን ነገር መመልከታችን ይበልጥ አያስነቅፈን ? ምግብን ከመብላት ተከልክለሃልን? እንዲሁ ለሰውነትህ ጎጂ የሆኑ ነገሮችን በዐይንህም በጆሮህም ከመመገብ ተከልከል፡፡ ጆሮ የምትጦመው ለኃጢአት ከሚጋብዙ ክፉ ወሬዎችና ሐሜትን ከመስማት ነው፡፡ “ሐሰተኛ ወሬን አትቀበል ሐሰተኛ ምስክርም ትሆን ዘንድ ከኃጢአተኛ ጋር እጅህን አታንሣ፡፡”እንዲል(ዘጸአ.፳፫፥፩(23፡1))
አፍህም ከከንቱ ንግግር ይጡም ፡፡ ከአሣና በጦም ሰዓት መመገብ ከተከለከልናቸው የፍስክ ምግቦች ተከልክለን ወንድሞቻችንንና እኅቶቻችንን በክፉ ቃላችን ሕሊናቸውን የምናቆስልና በሐሜት ሥጋቸውን የምንበላ ከሆነ ከጦማችን ምን ዋጋን እናገኛለን? ክፉ ተናጋሪ የወንድሙን አካል ያቆስላል ሥጋውንም ይበላል፡፡ ስለዚህም ቅዱስ ጳውሎስ ይህን አስመልክቶ  እጅግ የሚያስደነግጥ ንግግርን ተናገረ “ሕግ ሁሉ በአንድ ቃል ይፈጸማልና እርሱም፡- ባልንጀራህም እንደ ራስህ ውደድ  የሚል ነው፡፡ ነገር ግን እርስ በእርሳችሁ ብትነካከሱና ብትበላሉ እርስ በእርሳችሁ እንዳትጠፋፉ ተጠንቀቁ፡፡(ገላ.፭፥፲፭(5፡15))ብሎ አስጠነቀቀን፡፡
ስለታሙ የሐሜት ጥርስህ የሚያርፈው በወንድምህ ሥጋ ላይ ሳይሆን ነፍስ ላይ ነው፡፡ በዚህም ጥርስህ ወንድምህን በእጅጉ ትጎዳዋለህ፡፡ እንዲህ በማድረግህ አንተም እርሱንም ሌሎችንም ብዙ ሺህ ጊዜ ትጎዳቸዋለህ፡፡ በሐሜትህ አንተን የሚሰማህ ባልንጀራህ የሐሜት ተባባሪ ይሆናል፡፡ በዚህም ምክንያት እርሱንም በደለኛ ታደርገዋለህ፡፡ እርሱም በእርሱ ላይ ከነገሠበት ኃጢአት የተነሣ ለሌላ ለወዳጁ ምን መርጦ ማውራት እንዳለበት ሳያውቅ ከሐሜተኞች ጎራ ይቀላቀላል፡፡እንዲህ ዓይነት ሰው ጻድቅ ልንለው እንችላለንን? እንዲህ ዓይነት ሰው  በመጦሙ ትልቅ የጽድቅ ሥራን እንደፈጸመ ቆጥሮ ይኩራራል፡፡ ሰዎችን ወደ ኃጢአት እየመራ ትልቅ ሥራን እንደሠራ ሰው ራሱን በከንቱ ያስኮፍሳል፡፡ ከዚህ ጎን ለጎን ሊታይ የሚገባው ትልቁ ቁም ነገር ስለቤተክርስቲያን ጥቅም ሲባል የእንዲህ ዓይነቱን ሰው ንግግር ከመስማት መከልከል እንደሚገባ ነው፡፡ ምክንያቱም የዚህ ሐሜተኛ ወሬ እርሱን ብቻ ኃጢአተኛ የሚያሰኝ ጉዳይ ሳይሆን ቤተክርስቲያንንም ጭምር የሚያሰድብ ነውና፡፡
ስለዚህ በጦም ሰዓታችሁ ጊዜም ይሁን አይሁን  ሦስት ነገሮችን በሕሊናችሁ ትይዙ ዘንድ እመክራችኋለሁ፡፡ እነርሱም ክፉ ከመናገር መከልከልን፣ ማንንም ሰው እንደጠላት ከማየት መቆጠብንና እንደልምድ አድርጋችሁ ከያዛችሁት መሐላ ትርቁ ዘንድ እመክራቸኋለሁ፡፡
በአጨዳ ላይ ያለ ገበሬ እህሉን ከእርሻው ላይ በአንዴ እንዳይሰበስብ ነገር ግን ጥቂት በጥቂት እንዲሰበስብ እኛም እነዚህን ምክሮች ተግባራዊ በማድረግ በዚህ የጦም  ወቅት ልንለማመዳቸው እና መልካም ልምዶቻችን ልናደርጋቸው ይገባናል፡፡ እንዲህም በማድረጋችን በቀላሉ መንፈሳዊ ጥበብን ገንዘባችን ማድረግ ይቻለናል፡፡ በዚህም ዓለም ሳለን መልካም ተስፋ ያለውን አዝመራ እናፈራለን፡፡በሚመጣውም ዓለም በክርስቶስ ፊት ያለፍርሃት በደስታ ተሞልተን እንድንቆም ይረዱናል፡፡ ለእግዚአብሔር መንግሥት የሚያበቃንን ጸጋ አግኝተን የክብሩ ወራሾች ያድርገን፤ ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ ክብር ምስጋና ይሁን ዛሬም ዘወትርም እስከዘላለሙ አሜን፡፡
 ጦም የጤንነት እናት፣ የፍቅር እኅት፣ የትሕትና ወዳጅ ናት፡፡ ሕመሞች አብዛኛውን ጊዜ ያለቅጥ ከመመገብ የሚመነጩ ናቸው፡፡ (ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ)
ከምግባራት ሁሉ ታላቁ ጸሎት ነው ነገር ግን የእርሱ መሠረቱ ጦም ነው፡፡የምንጦምበት ምክንያት ርኩስ የሆነውን የሰይጣንን መንፈስ በነፍሳችን ውስጥ እንዳያድር ለመጠበቅ ነው፡፡ ሥጋችንን ለጦም ባስገዛነው ጊዜ ነፍሳችን ነፃነትን፤ ጥንካሬን ሰላምን ፣ንጽሕናን እንዲሁም እውቀትን ለመለየት እንድትበቃ ትሆናለች፡፡ (ጻድቁ ዮሐንስ ዘክሮስታንድ)
እውነተኛ ጦዋሚ ራሱን ከክፉ ምግባራት የከለከለ፤ ከንቱ የሆኑ ንግግሮችን ከመናገር የተቆጠበ፣ ሐሰትን የማይናገር፣ ሐሜተኛ ያልሆነ፣ በማንም ላይ የማይፈርድ፣ሽንገላን የማይወድና እኒህንም ከመሰሉ ነገሮች ራሱን የተጠበቀ ፣የማይቆጣ፣ የማይበሳጭ ፣ተንኮለኛ ያልሆነ ፣ ቂመኛ ያልሆነና፣ እነዚህን ከመሳሰሉ ክፋቶች ሁሉ የራቀ ሰው ነው፡፡
ሕሊናህ ኃጢአትን  ከማሰብ ይጡም፡ አእምሮህም ኃጢአትን ከማስታወስ ይከልከል፡፡ ክፉን ከመመኘት ሁሉ ጡም፡፡ ዐይኖችህ ከንቱ የሆኑ ነገሮችን ከመመልከት፣ ጆሮህም ከንቱ ከሆኑ ዘፈኖችና ከሐሜተኞች ሹክሹክታዎች ጠብቅ፡፡ አንደበትህ ከሐሜት፣ በሌላው ላይ ከመፍረድ ፣ከስድብ፣ ከውሸት ፣ከማታለል፣ከሽንገላ ንግግሮች እንዲሁም ከማይጠቅሙና አጸያፊ ከሆኑ  ቃላት ይጡሙ፡፡ እጆችህም ሰውን ከመግደልና የሌላውን ንብረት ከመዝረፍ ይጡሙ፡፡ እግሮችህም ኃጢአትን ለመፈጸም ከመሄድ ይጡሙ፡፡ ከክፉ ተመለስ መልካምንም ፈጽም፡፡ (ቅዱስ ኤፍሬም)
 ጦም ምን እንደሚያደርግ ትመለከታለህን? ሕመምን ይፈውሳል ፣አጋንንትን ያስወጣል፣ ክፉ አሳቦችን ከአእምሮ ያስወግዳቸዋል፣ ልብንም ንጹሕ ያደርጋታል፡፡ አንድ ሰው በክፉ መንፈስ የተያዘ ቢሆን  እንዲህ ዐይነት መንፈስ በጦምና በጸሎት እንደሚወጣ ያስተውል፡፡ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ “ይህ ዓይነት ግን ከጸሎትና ከጦም በቀር አይወጣም” እንዳለው (ማቴ. ፲፯፥፳፩(17፡21)) (ቅዱስ ቲክሆን)
የአርባ ቀን ጦም የሥጋ ፍትወታትን ይገድላቸዋል፣ቁጣንና ብስጭትን ከሰውነታችን ያስወግዳቸዋል፣  ከሆዳምነት ከሚመነጩ የትኞቹም ነገሮች ሁሉ ነፃ ያወጣናል፡፡ በበጋ ወራት ፀሐይ ከነሙሉ ኃይሉዋ እንድትወጣና ምድርንም በሙቀቱዋ እንደምታግል በላዩዋም የበቀሉ አትክልቶችን እንደምታደርቅ፤ ከሰሜን የሚነፍሰውም ነፋስ የደረቁትን ሳሮች እንደሚጠርጋቸው፤  እንዲሁ በጦም ወቅትም አብዝቶ በመመገብ የበቀሉትን የሥጋ ፍትወታት ይወገዳሉ፡፡ (ቅዱስ አትናቴዎስ)
ቅዱሳን ጠዋሚዎች ጽኑ ወደሆነው የጦም ሥርዓት የገቡት ወዲያው አይደለም፡፡  በጥቂት ምግብ ወደ መጥገብ የመጡት ቀስ በቀስ ነው፡፡ እነዚህ ቅዱሳን ኃጢአትን ፈጽመው አያውቋትም፡፡ ሁልጊዜ ለመልካም ሥራ እንደተፋጠኑ ነው፡፡ በእነርሱ ዘንድ ሕመም አይታወቅም እድሜአቸውም  ከሰው ሁሉ በተለየ የረዘመ ነው፡፡ (ቅዱስ አግናጢዎስ)
ጦም  የሰውን እድሜ አያሳጥርም ፣ ቅዱስ ቄርሎስ ዘአንኮራይት በ108 እድሜው አረፈ፡፡ ቅዱስ እንጦስም 105 ዓመት ሙሉ ኖሮአል፡፡ ቅዱስ መቃርስ ዘእስክንድሪያ የኖረበት እድሜ 100 ዓመት ነበር ፡፡ (ቅዱስ አውግስጢኖስ)
አርባውን ቀን መጦምን ቸል አትበሉ፡፡ ምክንያቱም ክርስቶስን የምንመስልበት ሕይወት ከዚህ ጦም እናገኛለንና፡፡ (ቅዱስ እንጦስ) 
ወስብሐት ለእግዚአብሔር ለዘበቅዱሳኒሁ ይሴባሕ ይእዜኒ ወዘልፈኒ ወለዓለም ዓለም አሜን፡፡ ወአሜን ለይኩን ለይኩን፡፡   

Friday, September 13, 2013

saint moses the ethiopian

      Abraham, the disciple of Abba Agathon, questioned Abba Poemen, saying, “How do the demons fight against me?” Abba Poemen said to him, “The demons fight against you? They do not fight against us at all as long as we are doing our own will. For our own wills become the demons, and it is these which attack us in order that we may fulfill them. But if you want to see who the demons really fight against, it is against [Abba] Moses and those who are like him.


Abba Moses (Hymns and the 7 instructions)

”Seven instructions which Abba Moses sent to Abba Poemen. He who puts them into practice will escape all punishment and will live in peace, whether he dwells in the desert or in the midst of brethren.

1. The monk must die to his neighbor and never judge him at all, in any way whatever.

2. The monk must die to everything before leaving the body, in order not to harm anyone.

3. If the monk does not think in his heart that he is a sinner, God will not hear him. The brother said, ‘What does that mean, to think in his heart that he is a sinner?’ Then the old man said, ‘When someone is occupied with his own faults, he does not see those of his neighbor.’

4. If a man’s deeds are not in harmony with his prayer, he labors in vain. The brother said, ‘What is this harmony between practice and prayer?’ The old man said, ‘We should no longer do those things against which we pray. For when a man gives up his own will, then God is reconciled with him and accepts his prayers.’

The brother asked, ‘In all the affliction which the monk gives himself, what helps him?’ The old man said, ‘It is written, “God is our refuge and strength, a very present help in trouble.”’ (Ps-46.i)

5. The old man was asked, ‘What is the good of the fasts and watchings which a man imposes on himself?’ and he replied, ‘They make the soul humble. For it is written, “Consider my affliction and my trouble, and forgive all my sins.” (Ps.25.18) So if the soul gives itself all this hardship, God will have mercy on it.’

6. The old man was asked, ‘What should a man do in all the temptations and evil thoughts that come upon him?’ The old man said to him, ‘He should weep and implore the goodness of God to come to his aid, and he will obtain peace if he prays with discernment. For it is written, “With the Lord on my side I do not fear. What can man do to me?”’ (Ps. i 18.6)

7. A brother asked the old man, ‘Here is a man who beats his servant because of a fault he has committed; what will the servant say?’ The old man said, ‘If the servant is good, he should say, “Forgive me, I have sinned.”’ The brother said to him, ‘Nothing else?’ The old man said, ‘No, for from the moment he takes upon himself responsibility for the affair and says, “I have sinned,” immediately the Lord will have mercy on him.

The aim in all these things is not to judge one’s neighbor. For truly, when the hand of the Lord caused all the first-born in the land of Egypt to die, no house was without its dead.’

The brother said, ‘What does that mean?’ The old man said, ‘If we are on the watch to see our own faults, we shall not see those of our neighbor. It is folly for a man who has a dead person in his house to leave him there and go to weep over his neighbor’s dead.

To die to one’s neighbor is this: To bear your own faults and not to pay attention to anyone else wondering whether they are good or bad. Do no harm to anyone, do not think anything bad in your heart towards anyone, do not scorn the man who does evil, do not put confidence in him who does wrong to his neighbor, do not rejoice with him who injures his neighbor. This is what dying to one’s neighbor means. Do not rail against anyone, but rather say, “God knows each one.”

Do not agree with him who slanders, do not rejoice at his slander and do not hate him who slanders his neighbor. This is what it means not to judge. Do not have hostile feelings towards anyone and do not let dislike dominate your heart; do not hate him who hates his neighbor. This is what peace is: Encourage yourself with this thought, “Affliction lasts but a short time, while peace is for ever, by the grace of God the Word. Amen.” ‘

Friday, September 6, 2013

ቅዱስ ሩፋኤል ጦቢት እና ጦቢያ

ስለዚህ እንግዶችን መቀበል አንርሳ፡፡ በዚህም ምክንያት አንዳንዶች ሳያውቁ የመላእክትን እንግድነት ተቀብለዋልና፡፡ ዕብ. 13.1-2 ፡፡
በየዓመቱ ጳጉሜ 3 የቅዱስ ሩፋኤል መልአክ መታሰቢያ ነው ፡፡ ቅዱስ ሩፋኤል የጦቢትን ዓይን ያበራና ወለተ ራጉኤልን ተቆራኝቷት ከነበረው ጋኔን ያላቀቃት መሆኑ በመጽሐፈ ጦቢት በስፋት ተገልጿል፡፡
ጦቢት በፋርስ ንጉሥ በስልምናሶር ዘመን የተማረከ ከነገደ ንፍታሌም የተወለደ ጽኑዕ እሥራኤላዊ ነው፡፡ እግዚአብሔር በስልምናሶር ፊት የመወደድን ግርማና ባለሟልነትን ስለ ሰጠው አለቃ አድርጎ ሾሞት ነበር፡፡ ለወገኖቹ ምጽዋት በመስጠት ሕገ ርትዕን በመሥራት የተጋ ሰው ነበር፡፡ ሐና የምትባል ሚስት አግብቶ አንድ ልጅ ወልዷል፡፡ ስልምናሶር ሞቶ ሰናክሬም በነገሠ ጊዜ ከሹመቱ ስለሻረው ደግሞ ወደ ምድያም መሔድ አልቻለም፡፡
ሣራ ወለተ ራጉኤል ከፍተኛ ችግር ደርሶባት ነበር፡፡ ችግሯም ሕፃናት ወልጄ ቤት ንብረት ይዤ እኖራለሁ በማለት ባል አገባች ነገር ግን በዚች ሴት አስማንድዮስ የሚባል ጋኔን አድሮ ያገባችውን ሰው ገደለባት ሌላም ባል ብታገባ ሞተባት እንደዚህ እየሆነ በጠቅላላ ሰባት ድረስ ያሉትን ባሎችን ገደለባት፡፡

የራጉኤል ልጅ ሣራ በዚህ ሁኔታ በኀዘን ተውጣ ስትኖር በነበረበት ጊዜ ጦቢት ሸምግሎ ስለ ነበር ልጁ ጦብያን ጠርቶ በዚህ ዓለም እስካለ ድረስ ሊሠራው የሚገባውን መንፈሳዊ ሥራ እንዲሠራ በጥብቅ ከመከረው በኋላ በመጨረሻ ልጄ እኔ ሳልሞት የኑሮ ጓደኛህን ፈልግ፣ ስትፈልግም ዕወቅበት፣ እኛ የአብርሃም የይስሐቅና የያዕቆብ ዘሮች ነን ስለዚህ ከእነርሱ ወገን የሆነችውን እንድታገባ ከዚህም ሌላ ከገባኤል ዘንድ በአደራ ያስቀመጥኩት ገንዘብ አለና እኔ በሕይወት እያለሁ ብታመጣው የተሻለ ነው አለው፡፡
ጦብያም ያባቱን ምክር ሁሉ በጽሞና ካዳመጠ በኋላ ‹አባባ የነገርከኝን ነገር ሁሉ በተቻለኝ መጠን እፈጽማለሁ ግን ከገባኤል ጋር ስላለው ገንዘብ እንዴት ለማምጣት እችላለሁ? ሀገሩን አላውቀውም› አለው፡፡ በዚህ ጊዜ ነገሩ አሳሳቢ ሆኖ ስላገኘው ጦቢት ልጁ ጦብያን ‹አብሮህ የሚሄድ ሰው እስቲ ፈልግ ምናልባት አብሮ የሚሄድ ጓደኛ ታገኝ ይሆናል ደመወዝም ሰጥተን ቢሆን ካንተ ጋር የሚሄድ አንድ ሰው ግድ ያስፈልግሃልና ሂድ ሰው ፈልግ› አለው፡፡
ጦቢት ስንቃቸውን አስይዞ ጦብያ ቅዱስ ሩፋኤል ሸኛቸው
አብሮት የሚሄደው ሰው ለመፈለግም ቢሄድ አንድ መልካም ጐበዝ አገኘ ይኸውም መልአኩ ቅዱስ ሩፋኤል ነው፡፡ጦብያ ግን መልአኩ ቅዱስ ሩፋኤል መሆኑን ፈጽሞ አላወቀም ነበር፡፡ ይሁን እንጂ ጦብያ መልአኩን ሰው መስሎ እንዳገኘው ‹የሜዶን ክፍል ወደ ምትሆነውና ራጌስ ወደ ምትባለው ሀገር ከእኔ ጋር ለመሄድ ትችላለህን የድካምህን ዋጋ የጠየቅኸውን ያህል እሰጥሃለሁ› ሲል ጠየቀው ቅዱስ ሩፋኤልም ‹እሺ ካንተ ጋር ለመሄድ ፈቃኛ ነኝ መንገዱንም ሆነ ሀገሩን በሚገባ አውቀዋለሁ ከገባኤል ቤት ብዙ ጊዜ ኑሬአለሁና› አለው፡፡
ከዚህ በኋላ ጦብያ በል ከአባቴ ጋር ላስተዋውቅህ ብሎ ወደ አባቱ ወስዶ አስተዋወቀው ከእኔ ጋር የሚሄደው ሰው ይህ ነው በማለት ካስተዋወቀው በኋላ ጦቢትም ከወዴት እንደ መጣ ማን ተብሎ እንደሚጠራ ጠየቀው፡፡ መልአኩ ቅዱስ ሩፋኤልም የታላቅ ወንድምህ ወገን ከመሆንም ሌላ ስሜም አዛርያስ ይባላል አለው፡፡ ጦቢ. 5.12 ፡፡ ጦቢትም የወንድሙ ዘመድ መሆኑን ከሰማ በኋላ ‹አንተስ ወንድሜ ነህ በል የልጄ የጦብያን ነገር አደራ ከሀገር ወጥቶ አያውቅምና እንዳይደነግጥ ደኅና አድርገህ እንድትይዝልኝ› ብሎ ስንቃቸውን አስይዞ ሸኛቸው፡፡
አዛርያስ /ቅዱስ ሩፋኤል/ በመንገድ ይመራው ነበር፡፡ በዚህም ቅዱስ ሩፋኤል ‹መራኄ ፍኖት› /መንገድ መሪ/ ይባላል፡፡ እነርሱ ሲሄዱ ውለው ማታ ጤግሮስ ከተባለው ታላቅ ወንዝ ደረሱና ከዚያም ለማደር ወሰኑ፡፡ በዚህ ጊዜ ከድካሙ ጽናት የተነሣ ጦብያ ሊታጠብ ወደ ወንዙ ወረደና ልብሱን አውልቆ መታጠብ ሲጀምር አንድ ዓሣ ሊውጠው  ከባሕር ወጣ፡፡ ወዲያውም መልአኩ ቅዱስ ሩፋኤል ጦብያን ያዘው ፤ ዓሣውን እንዳትለቀው አለው ፤ ጦቢያም ከዓሳው ጋር ግብ ግብ ገጥሞ እየጐተተ ወደ የብስ አወጣው ፡፡ከዚህ በኋላ ቅዱስ ሩፋኤል ጦብያን እንዲህ ሲል አዘዘው፡፡  ዓሣውን እረደው ጉበቱንና ሐሞቱን ተጠንቅቀህ ያዘው ሌላውን ግን ጠብሰን እንበላዋለን አለው፡፡
ጦብያም መልአኩ እንዳዘዘው ዓሣውን አርዶ ሐሞቱንና ጉበቱን ያዘ
ጦብያም መልአኩ እንዳዘዘው ዓሣውን አርዶ ሐሞቱንና ጉበቱን ያዘ፣ ሌላውን ሥጋውን ግን ጠብሰው ራታቸው አደረጉት፡፡ ጦብያም ያንን የዓሣውን ጉበትና ሐሞት ለምን እንደሚያገለግል ለመረዳት ‹ይህን ያዘው ያልከኝ ለምንድን ነው?› ሲል ጠየቀው ቅዱስ ሩፋኤልም ጋኔን ያደረበት ሰው ሲገኝ ይህንን ከዕጣን ጋር ቢያጤሱበት ጋኔኑ ይለቃል ሲል መለሰለት፣፡
በዚህ ሁኔታ አንድ ባንድ ሲነጋገሩ ከቆዩ በኋላ መልአኩ ቅዱስ ሩፋኤል ጦብያን ‹ዛሬ ከራጉኤል ቤት እናድራለን፡፡ እርሱ ዘመድህ ነው፡፡ የእርሱም ልጅ ሣራ የምትባል ቆንጆ ልጅ አለችው፡፡ እሷን ለሚስትነት ይሰጥህ ዘንድ ለራጉኤል እነግርልሃለሁ› አለው፡፡
ጦብያም ‹ያች ልጅ ከዚህ በፊት ሰባት ሰዎች እንዳገቧትና ሰባቱም ባገቧት ሌሊት ደርቀው /ሞተው/ እንደሚያድሩ ሰምቻለሁ፡፡ ስለዚህ እኔ ላባቴና ለእናቴ አንድ ልጅ ነኝ እርስዋን አግብቼ ከዚህ በፊት እንዳገቧት ሰዎች እኔም የሞትኩ እንደሆነ አባቴንና እናቴን የሚረዳቸው የለም ቢሞቱም የሚቀብራቸው አያገኙምና እፈራለሁ› አለው፡፡ መልአኩ ቅዱስ ሩፋኤል ግን  ‹አባትህ ከዘመዶችህ ወገን ካልሆኑ በስተቀር ሌላ ሴት እንዳታገባ ሲል የነገረህን ረሳኸውን? በል ሰባት ባሎቿ ሙተውባታል ስለምትለው እኔ መድኃኒቱን አሳይሃለሁ ፤ አይዞህ አትፍራ አትሞትም የዓሣውን ሐሞትና ጉበቱን ለምን መሰለህ ያዘው ያልኩህ ? እንግዲህ ሐሞቱንና ጉበቱን ከዕጣን ጋር  ጨምረህ ስታጤስበት በሣራ አድሮ የነበረው አስማንድዮስ የተባለው ጋኔን ወጥቶ ይሄዳል ፈጽሞም ወደ እርሷ በገባህም ጊዜ ሁለታችሁ ይቅር ባይ ወደ ሆነው እግዚአብሔር ጸልዩ እርሷም የተዘጋጀች ናት፡፡ ከእኛ ጋርም ወደ ሀገርህ ይዘናት እንሄዳለን› አለው፡፡ ጦብያም ይህንን ቃል በሰማ ጊዜ ደስ አለውና ከእርሷ በስተቀር ሌላ እንዳያገባ በሙሉ አሳቡ ወሰነ፡፡
ከዚህ በኋላ ወደ ራጉኤል ቤት እንደ ደረሱ ሣራ በደስታ ተቀበለቻቸው የሣራ አባትም ጦብያን ገና እንዳለው ሚስቱ አድናን ‹ይህ ልጅ የእኔ ዘመድ ጦቢትን ይመስላል› አላት ከዚያም ጋር አያይዞ ‹ልጆች ከየት ሀገር መጣችሁ?› አላቸው፡፡ እነሱም ‹ከነነዌ ሀገር ነው የመጣን› አሉት፡፡ ‹ከዚያም ሀገር ጦቢት የሚባል ወንድም ነበረኝ ታውቁት ይሆን?› ሲል ጠየቃቸው፡፡ በዚህ ጊዜ ጦቢያ አባቱን ሲጠራለት ‹እናውቀዋለን፡፡ እኔም ራሴ የጦቢት ልጅ ነኝ› አለው፡፡ ከዚያ በኋላ ራጉኤል ‹የወንድሜ ልጅ ነህን?› ብለ እቅፍ አድርጐ ሳመው፡፡ አድናም ሳመችውና ሁሉም ተያይዘው የናፍቆት ልቅሶ ተላቀሱ፡፡ ከወንድሙ እንደ መጡም ሲገነዘብ በግ አርዶ በጥሩ ሁኔታ ጋበዛቸው፡፡
ራትም ከበሉ በኋላ ጦብያ ቅዱስ ሩፋኤል በመንገድ የነገረውን በልቡ ሲያወጣ ሲያወርድ ስለ ዋለ  ቅዱስ ሩፋኤልን ያንን በመንገድ የነገርከኝን አሁን ፈጽምልኝ ሲለው ሰምቶ ስለ ልጅቷ መሆኑን ስለ ገባው ራጉኤል ጦብያን ‹ልጄ ይህች ልጅ ላንተ የምትገባ ናት ሰጥቸሃለሁ አይዞህ አትጠራጠር አሁንም ብላ ጠጣ ለዛሬም ደስ ይበልህ አለውና ሣራ ካለችበት የጫጉላ ቤት አግብተው ዘጉት፡፡ ጦብያም ሣራን በይ እኅቴ ኑሮዋችን እንዲቃናልንና ጋብቻችን እንዲባረክልን አስቀድመን ወደ ፈጣሪያችን ጸሎት እናድርግ› አላትና አብረው ጸሎት ካደረጉ በኋላ ያንን የያዘውንና የዓሣ ጉበትና ሐሞት ከዕጣን ጋር ጨምሮ ቢያጤስበት በሣራ አድሮ ባሎችዋን ይገድልባት የነበረው አስማንድዮስ የተባለው ጋኔን ከሣራ ለቆ ወጥቶ ሄደ ሁለተኛም ሊመለስ አልቻለም፡፡ እነርሱም በሰላምና በጤና አደሩ፡፡ የጦብያንና የሣራን ጋብቻ የባረከ ቅዱስ ሩፋኤል ስለሆነ ‹መልአከ ከብካብ› ይባላል፡፡
ከዚያ በኋላ የጤንነታቸውን ነገር ሲረዱ የሰርጉ ቀን የሚሆን የ14 ቀን በዓል እስኪፈጸም ድረስ ጦብያ ወደ ሀገሬ እሄዳለሁ ብሎ እንዳያውከው በማለት አማለው፡፡
ጦብያ የዓሣውን ሐሞትና ጉበቱን ይዞ ስለ ነበር የአባቱን ዓይን ቀባው ወዲያውም ዓይኖቹ ተከፈቱ
የ14 ቀን በዓለ መርዓ ከተፈጸመ በኋላ ግን ጥሬ ገንዘብና የከብት ስጦታ አድርጐ መርቆ ወደ ሀገሩ ሰደደው፡፡ ወላጆቹ ጦቢትና አድና ግን በመዘግየቱ ልጃችን ምን አግኝቶት ይሆን? እያሉ ለጊዜው ሳያዝኑ አልቀሩም፡፡ ከጥቂት ቀናት በኋላ ሚስቱንና ግመሎቹን ይዞ ሲመጣ በክብርና በደስታ ተቀበሉት፡፡ የጦብያ አባት ጦቢትም ልጅህ መጣ ሲሉት ዓይነ ሥውር ስለ ነበር እርሱን እቀበላለሁ ሲል ስለ ወደቀ ወዲያው ጦብያ የዓሣውን ሐሞትና ጉበቱን ይዞ ስለ ነበር የአባቱን ዓይን ቀባው ወዲያውም ዓይኖቹ ተከፈቱ፡፡
 የቅዱሳንን ጸሎት ከሚያሳርጉ ከሰባቱ ሊቃነ መላእክት አንዱ እኔ ሩፋኤል
ነኝ› ሲል ገለጠላቸው፡፡ እነርሱም ወድቀው የአክብሮት ስግደት ሰገዱለ
በመጨረሻም ከጦብያ ጋር ሄዶ የነበረው  መልአኩ ቅዱስ ሩፋኤልን የድካሙን ዋጋ ገንዘብ ለመስጠት ጠሩት እርሱ ግን ጦቢትንና ጦብያን ‹ፈጣሪያችሁን አመስግኑ እናንተ እስከ ዛሬ ድረስ ከየት እንደመጣሁ ማን እንደ ሆንኩ አላወቃችሁኝም፡፡ የእግዚአብሔር ምሥጢር ግን በክብር ሊገለጥ ይገባል እንጂ ሊሰውሩት ስለማይገባ የእኔን ተፈጥሮና ስም ልነግራችሁ እፈልጋለሁ ተፈጥሮዬ መልአክ ነኝ፣ ሥራዬም የቅዱሳንን ጸሎት ከሚያሳርጉ ከሰባቱ ሊቃነ መላእክት አንዱ እኔ ሩፋኤል ነኝ› ሲል ገለጠላቸው፡፡ እነርሱም ወድቀው የአክብሮት ስግደት ሰገዱለት፡፡ የአባቶቻቸውን አምላክ እግዚአብሔርንም አመሰገኑት፡፡ /መጽ. ጦቢት/፡፡
ስለዚህ እንግዶችን መቀበል አንርሳ፡፡ በዚህም ምክንያት አንዳንዶች ሳያውቁ የመላእክትን እንግድነት ተቀብለዋልና፡፡ ዕብ. 13.1-2 ፡፡
ጦቢት ከእህሉ ከፍሎ ለተራበ የሚያበላ ከልብሱ ለተራቆተ ሰው የሚያለብስ እግዚአብሔርን ዘወትር የሚያመሰግን ለወገኖቹ የሚራራ አሥራት በኩራት የሚያወጣ ሰው ነበር፡፡ በመሆኑም በሥራው ሁሉ እንዲረዳው በችግሩ ጊዜ እንዲያጸናው ቅዱስ ሩፋኤል ተልኮለታል፡፡ እኛም በሕይወታችን የጐደለብንን ነገር እንዲሞላልን ጐዳናችንን እንዲያስተካክልልን ከክፉ ጋኔን እንዲጠብቀን አምላክ ቅዱስ ሩፋኤል ተለመነን ቅዱስ ሩፋኤልንም አማልደን ማለትን ገንዘብ እናድርግ፡፡
ጳጉሜ የዘመን መሸጋገሪያ እንደ ሆነች ዕለተ ምጽአትም ወደ እግዚአብሔር መንግሥት የምንሸጋገርባት ስለሆነች ከወዲሁ የቅዱስ ሩፋኤልን የመታሰቢያ በዓሉን ስናከብር በአማላጅነቱ ከቅዱሳን ኅብረት እንዲደምረን በንስሐ ታጥበን ደጅ ልንጠና ይገባል፡፡ 
የቅዱስ ሩፋኤል ልመናው ይደረግልን በረከቱ ይደርብን፡፡ አሜን፡፡

Sunday, September 1, 2013

st Mamas the great martyr ቅዱስ ማማስ


Martyr Mamas of Caesarea in Cappadocia (275), and his parents, Martyrs Theodotus and Rufina
September 2

He began his life in the cruellest of circumstances: both of his parents were imprisoned for their faith in Christ. First his father, Theodotus, died in prison, then his mother, Rufina, died shortly after his birth, so the infant was left alone in prison beside the bodies of his parents.

But an angel appeared to the widow Ammia, telling her to go to the prison and rescue the child. Ammia obtained the city governor's permission to bury the parents and bring the child home.

He was called Mamas because he was mute until the age of five and his first word was `Mama'. Despite his late beginning, he showed unusual intelligence and, having been brought up in piety, soon openly proclaimed his Christian faith.

When he was only fifteen years old he was arrested and brought before the Emperor Aurelian. The Emperor, perhaps seeking to spare the boy, told him to deny Christ only with his lips, and the State would not concern itself with his heart.

Mamas replied `I shall not deny my God and King Jesus Christ either in my heart or with my lips.' He was sent to be tortured, but miraculously escaped and lived in the mountains near Caesarea.

There he lived in solitude and prayer and befriended many wild beasts. In time, he was discovered by the persecutors and stabbed to death with a trident by a pagan priest.
ምንጭ holy father

Thursday, July 4, 2013

አቡነ ተክለ ሐዋርያት ዘደብረ ጽሞና ካልዕ


  
        በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን::
  አቡነ ተክለ ሐዋርያት ዘጽሞና ካልዕ ዘያበርህ አዕፋሩ የተባሉት ደገኛ አባት ትውልድ ሀገራቸው ሸዋ ደብረ ጽሞና የሆኑት በአጼ ዘርዓያዕቆብ የነበሩ በአባ አትናቴዎስ መቃብር ላይ ሄደው አጥብቀው የጸለዩ ፯ አክሊል የወረደላቸው ጌታ ተገልጾ ከጊዮርጊስና፤ ከዮሐንስ መጥምቁ ጋር ነው ክፍልህ ያላቸው ጻድቅ ናቸው። በዚህም ሙታን የተነሱላችሁ ብዙ ተዓምር ያደረጉ ብርሃን የወረደላቸው ታላቅ ጻድቅ ናቸው። ሲጸልዩ ነፍሴ ፫ (ሦስት) ነገርን ትፈልጋለች ይሉ ነበር። 1 ከዚህ ዓለም ሀሜት መራቅን 2 ክፉ ነገር ከማየት መራቅን 3 ከንቱ ነገር ከመስማት መራቅነ እያሉ ይማጸኑ ነበር። እንዲህ እያሉ በሚጸልዩበትም ወቅት መልአኩ መጣና ወደ በረሃ ምንም ሰው ወዳሌለበት ሂድ አላቸው። እንዳላቸው ወደ ምድረ ሐጋይ በዝዋይ አድርገው አልፈው ከባሕር ውስጥ ባለ ዋሻ ገቡ። ከዚያ ገብተው ይጸልዩ ጀመር። በዚያም ብርሃን ወርዶላቸው ነፍሴ ሰውነቴን ተጸየፈች እያሉ ይጸልዩ ጀመር። በዚያን ጊዜ ጌታ ተገልጾላቸው ቃል ኪዳን ገብቶላቸዋል። ለኢትዮጵያ መኩሪያ ነህ ሲል ታሪካቸውን በብጹህ አቡነ ባስልዮስ ትዕዛዝ በዜና ቤተ ክርስቲያን ጋዜጣ በ1945 እና 1946 ዓ.ም በወጣ ታሪካቸው በስፋት ተመዝግቦአል። በመጨረሻም አባታችን አቡነ ተክለ ሐዋርያት ሕዳር 27 ቀን በክብር አርፈዋል። መላዕክትም 5 ሆነው ወርደው ቀብረዋቸዋል። መጀመሪያ በደብረ ብርሃን ተቀብረው ከ13 ዓመት በኋላ በምዕራብ ሸዋ አህጉረ ስብከት ስር በምትገኘው ወደ ደብረ ፅሙና አፅማቸው መጥተዋል።

አባታችን አቡነ ተክለሐዋርያት ከሌሎች ፃድቃን ለየት የሚያደርጋቸዉ አንድ ዓመት የታመመ ህመምተኛ ሥጋወደሙ ወስዶ (ተቀብሎ ) ከህመሙ የተነሳ አስመለሰዉ ዲያቆኑ ያስመለሰዉን በእቃ ተቀበለዉ ። ደምና መግል የተቀላቀለበት ነበር አባታቺን አቡነ ተክለሐዋርያት ሰለ ስጋወ ደሙ ክብር በእለተ አርብ ሃሞትና ሆምጣጥዉን እንደ አጠጡት የወልድን የመስቀሉን መከራ አስበዉ ፈጣሪአቸዉን ከመዉደዳቸዉ የተነሳ ያንን ያስመለሰውን ግጥም አደርገዉ ጠጡት በዘያን ጊዜ ጌታችን ወደሳቸዉ መጥቶ ወዳጄ ተክለሐዋርያት ሆይ በሰዉ ፊት እዳከበርከኝ በሰማያዊ መላአክትና በምድራወዊ ፃድቃን ሰማእታት ፊት አከብርሃለሁ ብሎ ጣቱን አንስቶ በጣቱ ፊታቸዉን በባረከዉ ግዜ ፊታቸዉ እንደ ፀሐይ አበራ በፊቱም ላይ ያለዉ የፀሐይ ብረሃን በምድር ላይ ሁሉ ታየ ።
አንድ ዶሮ በሰበት ቀን ከባለቤቱ አምለጦ መጥቶ አስጥለኝ ብሎ ለመናቸዉ አሳቸዉ የዶሮዉን ባለቤት ሰንበት ነዉ አትረደዉ ቢሉት አልሰማ ሰላላቸዉ ያላቸዉን ሸማ (ልብስ ) ሰጥተዉ ከመታረድ አድነዉታል በስእሉ ላይ አንደሜታየዉ ።
ክብር ይግባዉና የኛ አምላክ የቅዱሳንን ሥራ አይተን ሰምተን አንብበን እነሱ የሰሩትን መስራት ባንችል እንኳን ተስፋ እድንቆርጥ አልተወንም ምንም እንኳን እነሱ የተጋደሉትን ተጋድሎ መጋደል ባንችል ደካሞች ብንሆን ይልቁንም እነሱን ብንቀበል በነሱ ስም አንድ ጽዋ ቀዝቃዛ ዉሃ ብንሰጥ የነሱን ዋጋ እደሚሰጠን ቃል ገባልን አንጂ ማቴ ፲ ፬፩ አቡነ ተክለ ሐዋሪያት መድህን ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ ግንባራቸው ላይ ጸሐይ ያተመባቸው ታላቁ አባት ናቸው ቅድስት ቤተክርስቲያንም ወር በገባ በ27 አስባቸው ትውላለች፡፡ የጻድቁ በረከታቸው ይደርብን አሜን
†እንግዲህ እነዚህን የሚያህሉ ምስክሮች እንደ ደመና በዙሪያችን ካሉልን፥ እኛ ደግሞ ሸክምን ሁሉ ቶሎም የሚከበንን ኃጢአት አስወግደን፥ የእምነታችንንም ራስና ፈጻሚውን ኢየሱስን ተመልክተን፥ በፊታችን ያለውን ሩጫ በትዕግሥት እንሩጥ፤ እርሱ ነውርን ንቆ በፊቱም ስላለው ደስታ በመስቀል ታግሦ በእግዚአብሔር ዙፋን ቀኝ ተቀምጦአልና።† ዕብ. ፲፪:፩-፪
  የአባታችን አቡነ ተክለ ሐዋርያት ረድኤታቸው፣ ጸሎታቸው፣ ቃል ኪዳናቸው አማላጅነታቸው ከሁላችንም ጋር ይሁን አሜን።
አሜን†††

 ዋቢ መጽሐፍት፡-
 የኢትዮጵያ ተወላጆች ቅዱሳን ታሪክ በሊቀ ብርሃናት መርቆሬዎስ አረጋ ፲፱፻፪ ዓ.ም ገጽ ፶፩-፶፪ (51-52)
 ሽንቁሩ ሚካኤል ከሚል መጽሐፍ
ወስብሐት ለእግዚአብሔር ለዘበቅዱሳኒሁ ይሴባሕ ይእዜኒ ወዘልፈኒ ወለዓለም ዓለም አሜን፡፡ ወአሜን ለይኩን ለይኩን፡፡

Monday, June 10, 2013

ጰራቅሊጦስ

  በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን::
ቤተ ክርስቲያናችን ከምታከብራቸው ዓበይት በዓላት መካከል አንዱ በዓለ ጰራቅሊጦስ ነው፡፡ ይህ በዓል ጌታችን በሚያርግበት ጊዜ ደቀመዛሙርቱን አንትሙሰ ንበሩ ሀገረ ኢየሩሳሌም እሰከ ትለብሱ ኃይለ እም አርያም ሉቃ 2449 ብሏቸው አርጎ ነበር፡፡ተናግሮ የማያስቀር ነውና ባረገ በ10ኛው በተነሣ በ50ኛው ቀን ጰራቅሊጦስን ሰዶላቸዋል ፡፡
ጰራቅሊጦስ ማለት ፡-
1/ናዛዚ (አፅናኝ) ማለት ነው ከመንፈስ ቅዱስ ሥራዎች አንዱ ያዘኑትን የተጨነቁትን በተለያየ ነገር ውስጥ ገብተው ግራ የተጋቡትን ሁለ ሰለሚያጽናና ናዛዚ ይባላል ፡፡
2/ከሣቲ (ምስጢር ገላጭ) ማለት ነው የተደበቀውን የሚገልጥ የረቀቀውን የሚያገዝፍ የተሰወረውን የሚያሳይ በመሆኑ ከሣቲ ( ምስጢር ገላጭ) ይባላል ፡፡
3/መጽንኢ (የሚያጻና) በተለያየ ሁኔታ ውስጥ ገብተው የሚባዝኑት ለመውደቅ የተፍገመገሙትን እንዳይወድቁ የሚደግፍና የሚያጸና በመሆኑ መጽንኢ (የሚያጸና) ይባላል ፡፡

4/ መንፅሂ (የሚያነፃ) ማለት ነው በኃጢአት የወደቁትን ከኃጢአታቸው የሚያነጻቸው ነውና መንጽሂ (የሚያነጻ) ይባላል ፡፡
5/ መሠተሰርየ (ይቅር ባይ )ማለት ነው በኃጢአት የወደቁትን የበደሉትን ተጸጽተው ንሰሃ ሲገቡ ይቅር የሚል በመሆኑ መሠተሰርይ ይቅር ባይ ይባላል ፡፡
6/መስተፈስሔ (ደስታን የሚሠጥ) ማለት ነው የተጨነቁት፤ ያዘኑትን፤ያለቀሱትን እንባቸውን የሚያብስና ደስታን የሚሰጥ በመሆኑ መስተፈሥሔ (ደስታን የሚሰጥ) ይባላል  ፡፡
በአጠቃላይ ጰራቅሊጦስ ማለት መንፈሰ ጽድቅ ፤መንፈሰ ሕይወት ፤ባሕርያዊ እስትንፋስ ፤ አካላዊ ሕይወት ፤አካላዊ እስትንፋስ ማለት ነው፡፡
ለምንድን ነው  ቆይቶ በአረገ በ10ኛው ቀን መንፈስ ቅዱስን የላከላቸው ቢሉ ፡-
Ø    10ኛ መዓረግ የተቀመጥን እኛ ነበርንና ወደ ክብራችን ወደ መዓረጋችን እንደመለሰን ለማጠየቅ ነው
Ø    ዳግመኛም 10ሩን ቃሊት ቢጠብቁ መንፈስ ቅዱስን የሚሰጥ መሆኑን ለማጠየቅ ነው፡፡
ሐዋርያት ድንግል ማርያምን ይዘው  በሚጸልዩበት  በማርቆስ እናት በማርያም ቤት ወአስተረአይዎሙ ልሳናተ እሳት ከፋሊት ከመ እሳትዘይትከፈል በእሳት አምሳል የተከፋፈለ መንፈስ ቅዱስ ወርዶላቸው የሚያውቁት ጸንቶላቸው የማያውቁት ተገልጾሊቸው ሁሉም ከሚያውቁት ቋንቋ በተጨማሪ የማውቁት ቋንቋ ተገልጾላቸዋል ፡፡
በአጠቃላይ ሐዋርያት የሰባ ሁለት  ቋንቋ ባለቤት ሆነው በአደባባይ ስለአምላካቸው በድፍረት መስክረዋል ፤ ስለ እውነት ሲሉ በአደባባይ መከራን ተቀብለዋል ፤ ፈሪዎች የነበሩት ሐዋርያት የመንፈስ ቅዱስ ኃይል በመታጠቃቸው እሳቱን ፤ግርፋቱን፤ስደቡን የሰይፍ ስለቱን ባለመፍራት እራሳቸውን አሳልፈው እየሰጡ የላይኛው ቤታቸውን አሳምረዎል ፤ ዛሬም በክብር የወርቅ መዝገብ ላይ ሰማቸውን አጽፈዋል ፤ ክብራቸው ይህ ብቻ ሳይሆን አምላካችን በሚመጣበት ወቅት በ12 ነገደ እስራኤል ላይ ለመፍረድ ይመጣሉ፡፡

እንግዲህ በዓለ ጰራቅሊጦስ እኛ ክርስቲያኖች የምናከብረው እንደ ሐዋርያት ምስጢር እንዲገለጥልን ፤እንዲያረጋጋን ፤ይቅር እንዲለን ፤እንዲያጽናናን ፤ደሰታን እንዲሰጠን ነውና ሁላችንም ከዚህ በረከት የታደልን እንድንሆን በዓሉን በንጽሕና በቅድስና ሆነን፤ነጭ ልብስ ለብሰን፤በሌሊት ወደ ቤተ ክርስቲያን በመሄድ ቅዳሴ በማስቀደስ ፤በዕለቱ በጎ ስራ በመሰራት ልናከብረው ይገባል፡፡

አምላከ ቅዱሳን እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን -  አሜን፡፡

አባ ኖብ

     በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን::
  የጻድቅ ሰው ጸሎት በስራዋ እጅግ ሐይል ታደርጋለች:: ያዕቆብ 5 : 16 
  ልብ ሰባሪው ክስተት  ንግስ. . . .እና. . .አንጋሽ
አባኖብ ኤል ነሐስይ(ABANOUB EL NAHEESY) በግብጽ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በቅድስናቸው ከፍተኛ ማዕረግ ካላቸው ቅዱሳን አንዱ ነው:: አባ ኖብ በደቡባዊ ግብጽ ልዩ ስሙ ንሒስ በተሰኘ ስፍራ የተወለደ ጻድቅ አባት ሲሆን አባቱ መቁራሬ እናቱ ማርያም ይሰኛሉ፡፡ በጥር 24 ቀን የተወለደው ኖብ እጅግ በጣም መንፈሳዊ ነበርና በተወለደ በአምስተኛ ቀኑ መልአክ ሲያነጋግረው ወላጆቹ ዓይተው በአንክሮ ይጠብቁት ነበር፡፡ ገና በ12 አመቱ ወላጆቹ በሞት በመለየታቸው በ14 ዓመቱ መነኮሰ፡፡
በዘመኑ የክርስቲያን ደም እንደ ውሃ የሚያፈስ ዲዮቅልጥያኖስ የተባለ ንጉስ ነግሶ ስለነበር ክርስቲያኖች ላይ መከራና እንግልት ያበዛ ነበር፡፡ አባ ኖብም የገፈቱ ግንባር ቀደም ተቋዳሽ ነበር፡፡ አባ ኖብ ወላጆቹ በሃብት የከበሩ ስለነበሩ የወላጆቹን ሀብት ለድሆች መጽውቶ ወደ ሞትና መከራ ተሰደደ፡፡ ዲዮቅልጥያኖስ በአንድ ጊዜ በመጋቢት 9 ቀን ከቀኑ 3 ሰዓት አምስት ሺህ ክርስቲያኖችን አንገታቸውን ሲቆርጥ አባ ኖብ ያጽናና ነበር፡፡ በኋላም የብረት ጋን ጥደው ዘይት፣ ሰም፣ ቅንጭብ፣ ቁልቋል አፍልተው ከዚያ ጨመሩት፡፡ አባ ኖብም ከፍላቱ ውስጥ ሆኖ ይፀልይ ነበር፡፡ ግን እንደ አናኒያ፣ አዛሪያና ሚሳኤል /ሲድራቅ፣ ሚሳቅ፣ አብድናጐም/ ምንም አልነካውም መልአኩ አዳነው እንጂ፡፡ የዚህ ጻድቅ እረፍት በ89 ዓመቱ በሐምሌ 24 ቀን ነው፡፡ ከሞተም በኋላ በሰኔ 6 ቀን ተአምራትን ሰርቶ በግንቦት 10 ቀን ማህበረ ኖብ ከተባሉት ከ350 ጋር ተሰውተዋል፡፡ በሀገራችን ኢትዮጵያ በአባ ኖብ ስም የተሰራ ቤተ-ክርስቲያን ብዛት 5 ነው፡፡
ስንቶቻችን ግን አባ ኖብን እናውቃቸዋለን?
በሰሜን ሸዋ በሰላሌ ሀገረ ስብከት በአሌልቱ ወረዳ በጎመን አገር እና በአብሮ አገር የሚገኘው የምዕራፈ ቅዱሳን አባ ኖብ ገዳም የተመሰረተው በ1735 ዓ.ም በዓፄ ሣህለ ስላሴ ሲሆን የሁለት መቶ ሰባ /270/ ዓመት ዕድሜ ያለው ጥንታዊ ቤተ ክርስቲያን ነው፡፡ ይህ ቤትክርስቲያን ዕዳሜ ጠገብ ቢሆንም የጠንታዊነቱን ያህል ግን ነገሮች የተመቻቹለት አይደለም፡፡ በግንቦት 10 ቀን 2005 ዓ.ም በንግስ በዓላቸው ላይ ተገኝቼ የታዘብኩትን እነሆ፡-
ችግሩ ከአባኖብ ቅዱስ ፀበል ይጀምራል፡፡ ወደ አባ ኖብ ቤተክርስቲያን ሲኬድ ቀድሞ የሚኘው ይህ ቅዱስ ፀበል ከተራራ ስር የሚፈልቅ ሲሆን ዙሪያው በትናንሽ ቁጥቋጦዎች እና ዕፀዋት የተከለለ ነው፡፡ ለመጠመቂያ ተብሎ የተሰራለት ምንም ነገር በስፍራው የለም፤ በዚህም ሳቢያ የአካባቢው ነዋሪ ለተለያዩ አገልግሎቶች ሲቀጠምበት፣ ከብቶች ሲጠጡ እንዲሁም አራዊት ሲፈነጭበት ይስተዋላል፡፡ “ከጓሮ ያለ ፀበል ልጥ ይነከርበታል” እንዲሉ ፀበል እንኳን መሆኑን የማያውቅ የአካባቢው ተወላጆች አጋጥመውኛል፡፡ ይህ ከየት መነጨ ቢሉ አንድም ስፍራው የተቀደሰ መሆኑን ካለማሳወቅ በሌላ በኩል ደግሞ ቦታው ያልተከለለ በመሆኑ ነው፡፡ አስቸጋሪውንና ድንጋያማውን ቁልቁለት አልፈን ከደረስንበት የአባ ኖብ ቅዱስ ፀበል ለቀን ወደ አባ ኖብ ቤተክርስቲያን ስናመራ የጠበቀን ሌላ ድንጋያማ ቁልቁለትና መጠነኛ ዳገት ነበር፡፡ መልከአ ምድሩ ፈፁም ግሸን ማርያምን ይመስላል፡፡ ተራራማ ነው፤ እጅጉን ለዓይን ይማርካል፡፡
ከቤተክርስቲያኑ ስንደርስ ገና ታቦት አልወጣም ነበር፡፡ የአካባቢው ጥቂት ነዋሪዎች እና ከአዲስ አበባ የመጡ እጅግ በጣም ጥቂት ምዕመናን በቤተክርስቲያኑ እንደ ለቀስተኛ ተቀምጠው የታቦቱን መውጣት በትካዜና በጉጉት ይጠብቃሉ፡፡ ድባቡ እጅጉን ልብ ይሰብራል፡፡ በቦታው የአባ ኖብን ዓመታዊ ንግስ ለማክበርና ከበረከታቸው ለመካፈል የተገኘው ምዕመን ብዛት በጣም በሚገርምና በሚያሳዝን ሁኔታ ሁለት መቶ እንኳን አይሞላም ነበር፡፡ በከተማ ባሉ አብያተክርስቲያናት ለዓመታዊ ቀርቶ በወራዊ በዓላት መንገድ የሚዘጋው፣ ቅጥርን የሚያጨናንቀው ሕዝብ እዚህ የለም፡፡ ቆሞስም ሆነ ጳጳስ እዚህ የለም ከተማው ሙሉ የሚከተላቸው ሰባኪያን የሉም፣ ዘመሪ የለም፣ መዝሙር የለም፣ የሰንበት ተማሪ አጀባ የለም፣ ነዳይ /የኔ ቢጤ/ እንኳን የለም፡፡ የኔ ቢጤውስ ምፀዋት ከማን ሊጠይቅ ይኖራል? ሁኔታዉ እጅግ ያሳዝናል፡፡ ሰው የሌለው ቦታው ስለራቀ ይሆን? ብዬ እራሴን ጠየኩ፡፡ የሚገርመው ከቅርብ ጊዜያት ጀምሮ ሰው እየጐረፈ ያለባቸው የኩክ የለሽና የጻድቃኔ ማርያም ገዳማት ከአባ ኖብ ቤተክርስቲያን አንጻር ሲታዩ እሩቅ ናቸው፡፡ የአባ ኖብ ቤተክርስቲያን አልፈን ነው ኩክ የለሽና ጻድቃኔ ማርያም የምንሄደው፡፡
አሁን ታቦቱ ወጥቷል፤ ሊያነግስ የመጣው ሁለት መቶ የማይሞላው ሕዝብ በዝማሬ፣ በእልልታና በጭብጨባ አጀባው፡፡ የአባ ኖብ አምላክ ቅዱስ እግዚአብሔር ድንቅ ነው፤በጥቂት ሰዎች ደማቅ በዓል ተከበረ፡፡ የአባ ኖብ ገድል አስደናቂ ነው፤ ነገር ግን ገድላቸው እንኳን ተጽፎ የምናገኘው በልሙጥ ወረቀት በእጅ ጹሑፍ ነው፣ አልታተመም መታተሙም ይቅርና በኮምፒውተር አልተተየበም፡፡ የደብሩ አስተዳዳሪ እንደነገሩኝ ገድሉን እንዲት ሴት አሣትመዋለው ብለው ወስደው ከጠፉ በኋላ በጾምና በፀሎት በተዓምር ሊመለስ ችሏል፡፡ የካሕናቱ ኑሮ ያሳዝናል አርሶ አደሮች ስለሆኑ ቀድስው ወደ እርሻ፣ ከእርሻ ወደ አገልግሎት ይባክናሉ፡፡ የእንግዳ አቀባበላቸው ግን ድንቅ ነው፡፡ ከማዕዳቸዋ ሳይሰስቱ አርደው አብልተውናል፡፡ በጣም የደነቀኝ ለቤተክርስቲያኑዋ መደገፊያ ገንዘብ ሲሰበሰብ ካሕናቱም ከሌለው ምዕምን እኩል ይለግሱ ነበር፡፡ በከተማ ያልተዘብኩት አርአያ የሚሆን ልዩ ክስተት ነበር ለኔ፡፡ ጥንግ ድርብ፣ ያማረ መስቀልና መቋሚያ፣ መጎናፀፊያ፣ ጥምጣም፣ መጫሚያ ወዘተ . . .ሳያምራቸው እጃቸውን ለልግስና ይዘረጋሉ፣ ሰጥተው አርአያ ይሆናሉ ድንቅ አይደል ታዲያ ይሔ?
ሌላው የአባ ኖብ ቤተክስርቲያን ችግር መብራት ነው፡፡ በቦታው ጄኔሬተርም ሆነ በፀሐይ ኃይል የሚሰራ የኃይል ማመንጫ የለም፡፡ ይህም አልግሎቱን ፈታኝ ያደርገዋል፡፡ ቦታውን የሚረግጠው ጥቂት ምዕመን ለዓመት የሚበቃ ጧፍ የሚያበረክት ቢሆንም ችግሩን ግን አቃሎታል ማለት አይቻልም፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በቅዳሴ ጊዜ ወሳኝ የሆኑት እንዲሁም መገበሪያዎች እጣን፣ ዘቢብ፣ጧፍ፣ እና የመሳሰሉት በበቂ ሁኔታ ስለሌሉ ቅዳሴ እንዲታጐል እያደረጉ ይገኛሉ፡፡
እና ከእኔ፣ ከአንቺ እና ከአንተ ምን ይጠበቃል? ኦርቶዶክስ የሆነ ምላሹ ምንድነው? የተዋህዶ ልጅ ምን ይጠብቃል? አበው “ድር ቢያብር አንበሳ ያስር” ይላሉ፡፡ ኦርቶዶክስ የሆነ ሁሉ ልቡን ቢመልስ፣ ቢተባበር፣ ሐዘን ቢሰማው ይህን ታላቅ መንፈሳዊ ስፍራ መለወጥ ፣ ችግሩን መፍታትና ላላወቁት ማሳወቅ ይችላል፡፡
ማንም መኖሪያ ቤቱ ሲበላሽ፣ ሲራቆት፣ ሲፈርስ፣ የሃዘን ድባብ ሲያጠላበት የሚወድ የለም፡፡ ቤተክርስቲያንስ መንፈሳዊ ቤታችን አይደለችም? ጉዳቷ ያስደስተናል? በፍፁም፡፡ የቤተክርስቲያን ጉዳይ የረሳችን ጉዳይ ከሆነ እንተባበር፡፡ እኔ እጅግ ኃጢያተኛው ሰው ስሆን ይህን ተናግሬያለው፡፡
ቦታውን ለቀሪው የኦርቶዶክስ እምነት ተከታይ ለማሳወቅ ይረዳ ዘንድ እንዲሁም በችግሩ ዙሪያ ለመወያየት በቅርቡ መንፈሳዊ ጉዞ ወደ አባ ኖብ ቤተክርስቲያን ለማድረግ ሐሳቡ አለ፡፡ ሐሳቡ ወደ ተግባር የሚለወጠው የእኔ፣ የአንተና የአንቺ በጐ ፍቃድ ሲታከልበት ነው፡፡ ስለዚህ አስተያየታችሁን ስጡን፣እንብዛ፣እንተባበር፣ለስጋ ያልሆነ የነፍስና የጹደቅ ስራን በጋራ እንስራ በውጭም በአገር ውስጥም ያለው የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ልጅ በጋራ ከተነሳ የከበደው እንዲቀል፣ ተራራው እንዲናድ እናምናለን፤ መንፈሳችን ከእውነተኛው አምላክ ነውና፡፡
በአጠቃላይ በጉዳዩ ዙሪያ መረጃን የምትሹ እንዲሁም በጉዞው ላይ ተሳትፋችሁ ቦታውን ማየት የምትፈልጉ በ0911-33-43-47 ልታገኙን የምትችሉ መሆኑን እያሳወኩ በቀጣይ መደረግ ያለባቸውን ተግባራት ከደብሩ አስተዳዳሪና ከሌሎች ደጋፊ አካላት ጋር በመወያየት የማሳውቃችሁ መሆኑን እገልፃለሁ፡፡
የአባ ኖብ ቤተክርስቲያን የተመረጡ ብቻ የሚያዩት እና በነብር የሚጠበቅ ነው፡፡ እኔ በኃጢያት ያደፍኩ ሲሆን የመቅደላዊት ማርያም አምላክ መረጠኝ፣ እኔ ኃጢያተኛው ይህን ብያለው የአባታችን የአባ ኖብ ረድኤት፣ በረከት፣ ምልጃ ከሁላችንም ጋር ይሁን አሜን!
እግዚአብሔር ኃይል ነው!
ክብር ለድንግል ማርያም!
እባካችሁ ይህን ጹሐፍ ለሌሎች በማስተላለፍ (Share በማድረግ)ክርስቲያናዊ ግዴታዎትን ይወጡ!!!
 ፀሐፊ  ደረጄ ስዩም /ሚማገኤል/

Friday, May 31, 2013

ፃዲቁ አቡነ በግዑ


          በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን::
 የቅዱሳን ተጋድሎ ማውሳት ለመንፈሳዊነታችን ታላቅ አስተዋፅኦ አለው:: በየዕለቱ የምንሰማው የቅዱሳን ህይወትና ታሪክ እነርሱ ወደ ተጋደሉበት የቅድስና መንገድ የሚመራንና ለተሻለ የመንፈሳዊ ህይወት የምንጒዝበት ትልቅ ድልድይ ነው::

የጻድቅ ሰው ጸሎት በስራዋ እጅግ ሐይል ታደርጋለች:: ያዕቆብ 5 : 
 ጻድቁ አቡነ በግዑን ላስተዋውቆ በቤተክርስቲያናችን ታስበው ከሚውሉ ቅዱሳን መካከል ጻድቁ አቡነ በግዑ አንዱ ናቸው:: ለመሆኑ አቡነ በግዑ ማን ናቸው? ምንስ ተጋድሎ አደረጉ? ምንስ ቃል ኪዳን ተሰጣቸው? የሚለውን እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ እንመልከት መልካም ንባብ
ፃዲቁ አባታችን አቡነ በግዑ ቀድሞ በክፉ ስራ በኋላም በመልካም ተጋድሎ ፈጣሪው እግዚአብሔርን አገልግሏል፡፡ መጀመሪያ እንደ ሽፍታ በማታለል ከኖረ በኋላ ግን በብዙ ጾምና ፀሎት ወደ እግዚአብሔር ተመለሰ፣ ሲዘርፍና ሲቀማ ኖረ፣ ባማረ ልብሶች ሲያጌጥ ኖረ በኋላ ግን ጽድቅን እንደልብስ ለበሰ በጉልምስና ጊዜው ብርቱ ጠንካራ ስለነበረ ወደ እርሱ መቅረብ የሚችል አልነበረም፡፡ ብርቱ ጠንካራ ስለነበረ ወደ እርሱ መቅረብ የሚችል አልነበረም፡፡ የሀገሩ ሰዎች ሁሉ ይፈሩታል፡፡ በሰዎች ሁሉ ዘንድ የታወቀ ነበረ፡፡
አባታችን አቡነ በግዑ አስቀድሞ በስም ክርስቲያን ነበረ፡፡ ከዕለታት አንድ ቀን ቁርባን ሊቀበል ከህዝቡ ጋር ወደ ቤተክርስቲያን ሄደ፡፡ ካህኑ ባየው ጊዜ ከመንገድ አስገልሎ የህይወት ዘመንህን ሁሉ በከንቱ አሳለፍክ ዛሬ ስማ ልንገርህ በዘመን ፍፃሜ እግዚአብሔር ይጎበኝሃል፣ መንፈስ ቅዱስ ያድርብሃል ፍፁም መነኩሴ ትሆናለህ ከቤተሰቦችህም ተለይተህ ከፍ ወደ አለ ቤተክርስቲያን ትደርሳለህ በጾም በፀሎት በብዙ መከራም በዚያ ትኖራለህ አለው፡፡ ይህንንም በሰማ ጊዜ በእውነት ይደረግልኝ ይሆን? እያለ አሰበ የክርስቶስን ክቡር ስጋው ቅዱስ ደሙን ተቀብሎ ወደ ቤቱ ተመለሰ፡፡
ከዚያች ዕለት ጀምሮ እስከ መቼ በስንፍናዬ እኖራለሁ እስከ መቼስ የነፍሴን መዳኛ ሳላስብ እኖራለሁ እያለ ከዘመዶቹ ተለይቶ ከሀገር ወጥቶ ሄደ ኢዮ 40፡4 ቅዱስ እስጢፋኖስ ቤተክርስቲያን ገባ፡፡ ከመነኮሳት ማህበር ገብቶ እያገለገለ ከአንድ አረጋዊ መነኩሴ ጋር ኖረ፡፡ በጸም በፀሎትተወስኖ እግዚአብሔርን እያገለገለ በትንሽ በዓት ብቻውን ሆነ፡፡ በጾም ወራት ይኸውም በአብይ ጾም በህብስትና በውሃ ብቻ መጾም ጀመረ፡፡ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በተሰቀለበት ዕለት አርብ በህማማት ሳምንት ሁሉ ከንቱ ነው ብላሽ ነው የዚህ ዓለም አኗኗር ኃላፊ ነው የሚል የመጽሐፍ ቃል ሲነበብ ሰማ እንባው እንደውሃ እስኪወርድ ድረስ መሪር ልቅሶ አለቀሰ 1ዮሐ 2፡15 ከዚያች ቀን ጀምሮ ስጋዊ ስራን ተወ፡፡ ምግቡንም የዱር ዛፍ ፍሬና ቅጠል አድርጎ በተጋድሎ ውሃ ሳይጠጣ ኖረ፡፡
አበምኔቱና ቅዱሳን መነኮሳት ያለውሃ በመኖሩ የእግዚአብሔር ቸርነቱን አደነቁ፡፡ አባታችን አቡነ በግዑ አበምኔቱን አስጠርቶ ከበአቴ አልወጣም ብሎ በፈቃዱ ሁለት እጁንና ሁለት እግሩን በብረት ሰንሰለት አሰረ፡፡ አበምኔቱም ፈቀዱለት ባአቱንም በውስጥም በውጭም እጅ የሚያስገባ ትንሽ መስኮት በመተው በጭቃ መረጉት ይህም ለምግብ የሚሆን ቅጠል የሜዳ ጐመንና የዱር ፍሬ የሚገባበት ነው፡፡ አባታችን አቡነ በግዑ አፉን በጨርቅ አሰረ፡፡ በጾም በፀሎት ከእንባ ጋር ተጋድሎውን አደረገ፡፡ አበምኔቱ በትንሽ ልጅ የሚልኩለትን ቅጠል የኃጢአቱን ክርፋት እያሰበ ያለውሃ አብስሎ እስኪከረፋ ከአጠገቡ ያስቀምጠዋል ሽታውም ከአይነ ምድር ይከፋል፡፡ በጾመ በሶስተኛው ቀን ያን የከረፋ ቅጠል ይበላል በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ልደት በዓል ቀን ከበአቱ ወጥቶ በዮርዳኖስ ተጠመቀ፣ ቁርባንም ተቀብሎ አስቀድሞ እንደነበረው ወደ በአቱ ገባ፡፡ ከዚህ በኋላ ግን አልዘጋውም ለበአቱ ደጃፍ መዝጊያ አሰራ ቁርባን መቀበል አላቋረጠም፡፡
የአባታችን የአቡነ በግዑ ተጋድሎው ከውሃ ተከልክሎ የተቀበለው መከራ በሀገሩ ሰዎች ዘንድ ተሰማ፡፡ የሀገሪቱ ንጉስም በፀሎት አስበኝ ብሎ በመልክተኛ ልብስ ላከ ፃዲቁ አባታችን እንዲህ አለው የእግዚአብሔር ቸርነት ከአንተ ጋር ይሁን ይሄንን ልብስ አልቀበልም ለአንተም ለእኔም ወደ እግዚአብሔር እማልድ ዘንድ በዚህ ልብስ ፈንታ እጣን ላክልኝ አለው፡፡ ንጉሱም እንደተባለው አደረገ አባታችንም ዕጣኑን ለቤተክርስቲያን አገልግሎት ሰጠ፡፡ ምሳ 18 ፡ 12
ፃዲቁ አባት አቡነ በግዑ ውሃ መጠጣት ከተወ አምስት ዓመት ሆነው መቀመጥና በጎኑም መሬት ላይ መተኛት ተሳነው ስጋው አልቋልና፡፡ ከንፈሮቹም ከውሃ ጥም የተነሳ ደረቁ፣ ምላሱም ተጣበቀ፣ አይኖቹም በእንባ ደፈረሱ፣ አፍንጫውም ቆሰለ መገለ፣ መሄድም ተሳነው ሲወጣና ሲገባ በሁለቱ እጆቹና እግሮቹ ይድሃል፡፡ ቁርባን ሲቀበል ሁለት መነኮሳት አድርሰው ይመልሱታል፡፡ ይህን ጽኑ መከራ ከተቀበለ በኋላ ነፍሱን እንዲወስድ ወደ እግዚአብሔር ለመነ፡፡ የእግዚአብሔር መልአክ ተገልጦ በምሳሌ አስረዳው ከሞት ወደ ህይወት ትሻገር ዘንድ መከራውን ረኃቡንና ጥሙን ታገስ አለው፡፡ ያዕ 1 ፡ 12
አባታችን አቡነ በግዑ ይህን ሁሉ ተጋድሎ በእግዚአብሔር ኃይል አደረገ፣ ለሰባት አመት ውሃ ሳይጠጣ ኖረ፡፡ ከሰባት ዓመት በኋላ ከብዙ ረኃብና ጥም የተነሳ በጣም ታመመ፡፡ መናገርም ተሳነው፡፡ በመንፈስ ቅዱስ ኃይል ሰማያዊት ኢየሩሳሌምን ጎበኘ፡፡ የኃጥአን መኖሪያቸውን ተመለከተ፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ጋር አዕላፍ ቅዱሳንን ይዞ መጥቶ ስምህን ለጠራ፣ መታሰቢያህን ላደረገ፣ ወደ ተቀበርክበት ቦታ ሄዶ ለተሳለመ፣ በበአልህ ቀን ምጽዋት ለሰጠ እስከ ሰባት ትውልድ እምርልሃለሁ አለው ዳግመኛ በፀሎትህ አምኖ መልካም ስራ የሰራ የገድልህን መጽሐፍ የሰማ ሁሉ የእሳትን ባህር በግልጽ ይለፍ ብሎ ቃለ ኪዳን ገባላት፡፡
የእግዚአብሔር ሰው አቡነ በግዑ በአባታችን አቡነ ኢየሱስ ሞዓ እጅ ምንኩስናን ተቀበለ፡፡ አቡነ ኢየሱስ ሞዓን ዛሬ ግን ደክሜያለሁ መናገር ተስኖኛል፡፡ ነፍሴ ከስጋዬ መለያዋ ጊዜው ቀርቧል፡፡ መቃብር አስቆፍርልኝ አሁን ግን ወደ በዓትህ ተመለስ ብሎ አቡነ ኢየሱስ ሞዓ አሰናበተው ህመሙ ሲጠናበት አቡነ ኢየሱስ ሞዓ ተመልሰው መጡ፡፡ አቡነ በግዑንም ስለ ጽድቅ ብለህ እስከ ሞት ድረስ ተጋደልክ አሁን ግን ከእጅህም ከእግርህም ይህን የብረት ሰንሰለት እንፍታ አለው፡፡ የእግዚአብሔር ሰው አቡነ በግዑ ከሞትኩ በኋላ የታሰርኩበትን ሰንሰለት ፍቱት ፈቃድህ ከሆነ አሁን ፍታኝ ብሎ የብረት ሰንሰለቱ ተፈታ፡፡ ጥቂት ደቂቃ እንደቆየ ታህሳስ 27 ቀን አረፈ፡፡ መዝ 115/116 ፡ 6
የአባታችን የአቡነ በግዑ ረዴትና በረከት ይደርብን!!!
 ወስብሐት ለእግዚአብሔር ለዘበቅዱሳኒሁ ይሴባሕ ይእዜኒ ወዘልፈኒ ወለዓለም ዓለም አሜን፡፡ ወአሜን ለይኩን ለይኩን፡፡  
ፀሀፊ ገዛኸኝ ፈንታሁን       By gezahagn fantahun

Wednesday, May 22, 2013

ቅዱሳን መላእክት - ስግደት ለመላእክት


  • በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን::
    መስገድ የሚለው ቃል መዋረድ፣ ማጐንበስ፣ መንበርከክ፣ መደፋት፣ በግንባር መውደቅ፣ ግንባርን ምድር አስነክቶ መሬት ስሞ መመለስ ነው በማለት የአለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ መዝገበ ቃላት ያትታል፡፡ በቤተ ክርስቲያናችን ስግደት የአምልኮና የጸጋ ተብሎ ይከፈላል፡፡ የአምልኮ ስግደት ለእግዚአብሔር ብቻ የሚቀርብ ሲሆን የጸጋ ስግደት ደግሞ እግዚአብሔር ላከበራቸው ቅዱሳን ሰዎችና መላእክት የሚቀርብ ነው፡፡

    ለቅዱሳት መላእክት የምናቀርበው ስግደት ከላይ እንደተገለጸው የጸጋ ስግደት ነው፡፡ ጸጋ የሚለው ቃል በቁሙ ሲተረጎም ሀብት፣ መልካም ሥጦታ፣ ዕድል ፈንታ፣ ትምህርት፣ ብዕል፣ ክብር፣ ሞገስ የቸርነት ሥራ አለዋጋ የሚሰጥና የሚደረግ ማለት ነው፡፡[1] የጸጋ ስግደት ስንል እግዚአብሔር የሰጣቸውን ክብርና ሞገስ አምኖ መንበርከክ ነው፡፡ ይህም ራስን ለእግዚአብሔር ከማስገባት የሚመነጭ ነው፡፡

    ሰዶምና ገሞራን በእሳት ለማቃጠል የተላኩት መላእክት ወደ ሎጥ ቤት በገቡ ጊዜ ሎጥ በግምባሩ ተደፍቶ ለመላእክቱ እንደሰገደ ተጽፏል (ዘፍ. 19፥1)፡፡

    ኢያሱ ወልደ ነዌ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል በተገለጠለት ጊዜ በግምባሩ ተደፍቶ ለመልአኩ ሰግዶለታል፡፡ በዚህ ጊዜ ቅዱስ ሚካኤል የተቃውሞ አነጋገር አልተናገረም፡፡ ‹‹የቆምክባት ሥፍራ የተቀደሰች መሬት ናትና ጫማህን ከእግርህ አውጣ›› ከማለት በስተቀር (መጽ ኢያሱ 5፥13)፡፡

    የእሥራአል ንጉሥ የነበረው ነቢየ እግዚአብሔር ዳዊት ከእሥራኤል ሽማግሌዎች ጋር ከመሬት ከፍ ብሎ ሰይፉን ዘርግቶ ለተገለጠላቸው ለእግዚአብሔር መልአክ ሰግደውለታል (ዜና መዋዕል ቀዳ 21፥16)፡፡

    ነቢየ እግዚአብሔር ዳንኤል መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል በአባል ወንዝ አጠገብ በተገለጠበት ጊዜ ለመልአኩ ለቅዱስ ገብርኤል ራሱን ዝቅ አድርጐ በግንባሩ ወድቆ ሰግዶለታል፡፡ በዚሁም ላይ የግርማውን አስፈሪነት እና አስደንጋጭነት ጠቅሷል (ዳን. 8፥15)፡፡

    ከላይ የተገለጹት የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶች የሚያስገነዝቡን ለመላእክት ቅዱሳን ሰዎች እንዴት አክብረው እንደሰገዱላቸው ነው፡፡ ብርሃነ ዓለም ቅዱስ ጳውሎስ ‹‹የእግዚአብሐርን ቃል የተናገሩአቸሁን ዋሃቻችሁን አስቡ የኑሮአቸውንም ፍሮ እየተመለከታችሁ በእምነታቸው ምሰሉአቸው›› (ዕብ. 13፥7) እንዳለው የቅዱሳን አባቶቻችንና ሕይወት አኗኗር ዛሬ ለእኛ መመሪያ ሊሆነን ይገባል፡፡ እነርሱ አድርገው የተጠቀሙበትን ሁሉ እኛም እናደርገዋለን፡፡ እነርሱ ለቅዱሳን መላእክት ያላቸውን ፍቅርና አክብሮት በስግደት እንደገለጹ እኛም እግዚአብሔር ላከበራቸው ቅዱሳን መላእክት ፍቅራችንንና አክብሮታችንን በሥዕላቸው ፊት በመንበርከክ በመስገድ እንገልጻለን፡፡

    መላእክት ቢገለጡም ባይገለጡም ሕልውናቸው የተረጋገጠ ነውና ክብራቸው ያው ነው፡፡ ምናልባት አንዳንድ ሰዎች ሲገለጡ እንጂ ካልተገለጡ ሊሰገድላቸው አይገባም ሊሉ ይችላሉ፡፡ በዓይን ዓይቶ በእጅ ዳብሶ ከማመን ሳያዩ የሚያምኑ ብጹዓን እንደሆኑ ጌታችን አስተምል (ዮሐ. 2ዐ፥29)፡፡

    ስለዚህ እነዚህ ቅዱሳን አባቶች በዓይናቸው ዓይተው፣ በጆሯቸው ሰምተው ያደረጉትን እና ያመኑትን ለእኛ በማስተላለፋቸው እኛም የእነርሱን ዓይን ዓይን አድርገን ማእነርሱ አይተዋቸው የሰጡትን ክብር እንሰጣቸዋለን፡፡ መገለጣቸውና አለመገለጣቸው በእግዚአብሔር ዘንድ ያላቸውን ክብር አይጨምረውም አይቀንሰውምና ክብራቸው አንድ ነው፡፡ ስለዚህ ይሰገድላቸው ዘንድ የሚገባ ከሆነ ሲገለጡ ሳይገለጡ የሚል ሁኔታ መፈጠር የለበትም፡፡ ለእግዚአብሔር በመንፈስ የአምልኮት ስግደት እንደምንሰግድ ሁሉ (ዮሐ. 4፥24) እግዚአብሔር ባለበት ቦታ ሁሉ አብረው ለሚገኙት ቅዱሳን መላእክትም የጸጋ ስግደት በእምነት ማቅረብ ይገባል፡፡ እነርሱም እግዚአብሐር ባለበት ቦታ ሁሉ አሉና፡፡

    ራእ. 19፥10 (‹‹አትስገድልኝ››)

    አንዳንዶች ተጠራጣሪዎች ደግሞ ለመላእክት ሲገለጡም ሆነ ሳይገለጡ ምንም ዓይነት ስግደት አይገባቸውም በማለት ራእ. 19፥10 (‹‹አትስገድልኝ››) ላይ ያለውን ይጠቅሳሉ፡፡ በመሠረቱ ይህ ጥቅስ ለመላእክት የጸጋ ስግደት መስግድ እንደሚገባን እንጂ መስገድ እንደማይገባን የሚገልጽ አይደለም፡፡ ወንጌላዊውና ሐዋርያው ቅዱስ ዮሐንስ ለመልአኩ መስገዱ ሳያውቀው ሳይረዳው ያደረገው ድርጊት እንዳልሆነ እንድናምን ማንነቱና ሕይወቱ ያስገነዝበናል፡፡ ምክንያቱም የጥበብ፣ የማስተዋል፣ የዕውቀት ጸጋን የሚያድል መንፈስ ቅዱስ አድሮበት እያለ ሳያውቀው አደረገው ብሎ መናገርና ማመን መንፈስ ቅዱስን እንደ መጽረፍ /መስደብ/ ነው፡፡ በመንፈስ ቅዱስ የተቃኘ ሰው የሚያመልከውንና የሚሠራውን ሁሉ የሚያውቅ ነው፡፡ በተለይ ቅዱስ ዮሐንስ አካል ከሕልውና ተገልጾለት ምሥጢረ መለኮትን የተናገረ ታላቅ ሰው ሆኖ ሳለ ትንሿ ጉዳይ ተሰውራው ለመልአኩ ሳያውቅ ሰግዶ ተግሳጽ ደረሰበት ብሎ ማመን ሞኝነት ብቻ ሳይሆን ክህደትም ጭምር ነው፡፡ የመንፈስ ቅዱስን ሰላም ማቃለል ነው፡፡ «መንፈስ ቅዱስ የሰደበ ደግሞ ኃጢአቱ አይሠረይለትም፡፡» (ማቴ. 12፥31-32)፡፡

    የመልአኩ አነጋገር ታዲያ እንዴት ይተረጎማል? መልአኩ ቅዱስ ዮሐንስን አትስገድልኝ ማለቱ ስለ ሁለት ነገር ነው፡፡

    1ኛ. ስለ ትኀትና

    ዲያብሎስ ከሥልጣኑ የተሻረው ከክብሩ የተዋረደው በትዕቢቱ እንደሆነ የታወቀ ነው፡፡ ቅዱሳን መላእክት ግን ትሕትናን ገንዘብ ያደረጉ በመሆናቸው እንደ ሰይጣን ስገዱልን የሚሉ አይደሉም፡፡ ዳሩ ግን እግዚአብሔር ይከበሩ ዘንድ ፈቃዱ በመሆኑ የእግዚአብሔር ሰዎች እንዲወዷቸውና እንዲያከብåቸው አድርጓል፡፡ ለዮሐንስ በሰገደለት ጊዜ «አትስገድልኝ» ማለቱ በእግዚአብሔር ዘንድ የተጠላ ከአምልኮተ እግዚአብሔር የሚያወጣ ለጣኦት እንደመስገድ የሚያስቆጥር ሆኖ ሳይሆን መልአኩ ራሱን በዮሐንስ ፊት ዝቅ ከማድረጉ የተነሣ ስለ ትሕትና የተናገረው ነው፡፡ አንድ ሰው ሌላውን ሰው አክብሮ እጅ ቢነሣው /ከመቀመጫው ሲነሳና ሲቀበለው/ éረ አይገባም እንደሚለው ሁሉ ማለት ነው፡፡ ለዚሁም ማረጋገጫ የሚሆነን (ለትሕትና የተናገረ መሆኑን) በምዕራፍ 19 የሰጠውን ማስጠንቀቂያ በምዕራፍ 21 ላይ መድገሙ ነው፡፡ ለትሕትና የተናገረው መሆኑን ያወቀው ዮሐንስ ለመልአኩ ክብር መስጠት እንዳለበትና መስገድ እንደሚገባው ዐውቆ ድጋሚ ሲገለጥለት በድጋሚ ሰግዶለታል፡፡

    2ኛ ስለ ሥልጣነ ክህነት ክብር ሲል

    የቤተ ክርስቲያን የአጥቢያ ኮከብ ቅዱስ ጳውሎስ የካህናትን ሥልጣን አስመልክቶ ሲያስተምር #ካህናት ሰውን ሁሉ እንደሚዳኙ አታውቁምን? እናንተ ሰውን ሁሉ የምትዳኙ ከሆናችሁ ይህን ትንሹን ነገር ልትፈርዱ አይገባችሁምን? የዚህንስ ዓለም ዳኝነት ተውትና መላእክትን ስንኳ እንድንገዛ አታውቁምን$ (1ቆሮ 6፥2-3) ብሏል፡፡

    ከዚህ ትምህርቱ የምገነዘበው ካህናት በሥልጣናቸው መላእክትን ስንኳ ሳይቀር እንደሚያዙ ነው፡፡ ይህንንም ከቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ትምህርት እንረዳለን፡፡ በ344 ዓ.ም. በአንጾኪያ ከተማ የተወለደው ሊቁ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እምነትንና ፍቅርን፣ ትዕግሥትንና ትሕትናን፣ በአንድነት ገመድ አስሮ ሕዝቡን ለ7 ዓመት ወንጌልን ሰብኳል፡፡ በ387 ዓ.ም. በአንጾኪያ ከተማ ፖትርያርክነት ተሾሞ ሳለ አንድ ጉዳይ ይገጥመዋል፡፡

    ንጉሡ አርቃድዮስና ንግሥቲቱ አውዶክያስ ልጅ እየወለዱ እየሞተባቸው አላድግ ስላላቸው የዚህን ምክንያት ቢጠይቁ ደግ ሰው ክርስትና ባያነሣላችሁ ይሆናል ስላሏቸው ከዮሐንስ አፈወርቅ የበለጠ ደግ ሰው በዘመናችን አለን? በማለት ሴት ልጅ በወለዱ ጊዜ መጥተህ ክርስትና አንሣልን ብለው ላኩበት እርሱም ጥሪውን አክብሮ ሲሆድ በመንገድ ከእግዚአብሔር ዘንድ ከተላከ መልአክ ጋር ይገናኛል፡፡ የበቃ ነውና ረቂቁን መልአክ ሊያየው ችሏል፡፡ ዮሐንስም መልአኩን ‹‹ወዴት ትሄዳለህ?›› ብሎ ጠየቀው መልአኩም ሲመልስለት ‹‹አሁን አንተ የምትሄድባትን ብላቴና ነፍሷን ከሥጋዋ ለይተህ አምጣ ብሎኝ የታዘዝኩትን ለመፈጸም ወደዚያ መሄዴ ነው›› ይለዋል፡፡ ዮሐንስም ‹‹ቆየኝ በጥምቀት ሀብተ ውልድና፣ ስመ ክርስትና ከተሰጣት በኋላ የታዘዝከውን ትፈጽማለህ፡፡ እስከዚያው ግን ከዚሁ አትንቀሳቀስ›› ብሎት በሥልጣነ ክህነቱ ገዝቶት ሄደ፡፡ መልአኩም የዮሐንስን ግዝት ጠብቆ ባለበት ቆመ፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ልጅቷን ካጠመቃት በኋላ ንግቶት በሌላ መንገድ ተመለሰ፡፡

    የካህናት ሥልጣናቸው የማይናቅ፣ ትእዛዛቸውም ክብር የሚገባው መሆኑን ስለሚያውቅ ያ መልአክ ወደ ላይም ወደታችም ሳይል አሥር ዓመት ከዚያው ሥፍራ ቆሞ ኖረ፡፡ አሥር ዓመት ሲሆናት ለባል ታጨች ያጠመቅካት ብላቴና እነሆ ለአቅመ ሔዋን፣ ባል ልታገባ ነውና መጥተህ ባርከህ ስደዳት ብለው ለዮሐንስ አፈወርቅ ላኩበት፡፡ እርሱም በጥሪው መሠረት ከዛሬ አሥር ዓመት ልጅቱን ሊያጠምቅ ሲሔድ በሄደበት መንገድ መልአኩን ቆሞ አገኘው፡፡ «ምነው ከዚህ ቆመሃል?» አለው፡፡ መልአኩም ሲመልስለት «የካህናት ማዕረጋቸው የከበረ ነውና መች ወዲያ ወዲህ ያሰኛል፡፡ ቃልህን አክብሬ አንተ ቆይ ካልከኝ ወዲያና ወዲህ ብዬ አላውቅም» አለው ቅዱስ ዮሐንስም በዝንጉዕነቱ ራሱን ወቅሶ መልአኩን የታዘዘውን ያደርግ ዘንድ አሰናብቶታል፡፡

    ከላይ በተገለጸው ታሪክ ብናይ በፍጥሞ ደሴት መልአኩ ለዮሐንስ ወንጌላዊ አትስገድልኝ ማለቱ ዮሐንስ ካህንም ነውና ሥልጣኑ ሊያከብር እንደሚገባው ለመግለጽ ሽቶ ነው፡፡ በክብር ዮሐንስ ከመልአኩ ይበልጣልና፡፡
     ወስብሐት ለእግዚአብሔር ለዘበቅዱሳኒሁ ይሴባሕ ይእዜኒ ወዘልፈኒ ወለዓለም ዓለም አሜን፡፡ ወአሜን ለይኩን ለይኩን፡፡

Saturday, May 18, 2013

መንፈሳዊ ተጋድሎ





                                                              መንፈሳዊ ተጋድሎ ማለት ምን ማለት ነው?
መንፈሳዊ ተጋድሎ ማለት - አንድ ሰው የሚያምንበትን እምነት፣ የሚመራበትን ሕግ፣ የሚያልመውን ተስፋ እና የሚወደውን ነገር ተከትሎ ከግቡ ለመድረስ ማድረግ ያለበትን በማድረግ÷ ማድረግ የሌለበትን በመተው በነፃ ፈቃዱ ወስኖ፥ በሙሉ ልቡናው፥ በሙሉ ኃይሉ የሚያደርገው የውስጥና የውጭ መንፈሳዊ እንቅስቃሴ፥ ጥረትና ትግል ነው፡፡
 
  ሀ. ከፈቃደ ሥጋ ጋር የሚደረግ ውጊያ ነው፡፡
ሰው በዚህ ዓለም በተሰጠው ዘመኑ ራሱን ለፈጣሪው ለማስገዛት ከራሱ ጋር ብርቱ ተጋድሎ ማድረግ ግድ ይለዋል፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ ‹‹ሥጋ በመንፈስ ላይ መንፈስም በሥጋ ላይ ይመኛል፤ እነዚህም እርስ በርሳቸው ይቀዋወማሉ፡፡ ስለዚህም የምትወዱትን ልታደርጉ አትችሉም›› ብሎ የገለጸው ይህንን በሰው ሕይወት ውስጥ ያለውን የማያቋርጥ ጦርነት ነው፡፡ (ገላ 5፥12) ታላቁ አባት ኢዮብም ‹‹በምድር ላይ የሰው ሕይወት ብርቱ ሰልፍ አይደለምን ?›› በማለት ሰው ጽኑ ጦርነት የሚካሄድበት የጦር ሜዳ መሆኑን ገልጿአል፡፡ ይህም ጦርነት በተወሰነ ጊዜ ተነሥቶ የሚጠፋ ሳይሆን በሰው ዘመን ሁሉ የሚኖርና የዕድሜ ልክ ትግል ነው፡፡ ይህን የሥጋና የነፍስ ጦርነት በነፍስ አሸናፊነት ማጠናቀቅና ፈቃደ ሥጋን ድል አድርጎ ለፈቃደ ነፍስ ማስገዛት ይገባል፡፡
ይህ ሲባል ግን ሥጋ ርኵስ ነው፤ ሥጋ መጥፋትና መወገድ አለበት ማለት አይደለም፡፡ ሥጋ በራሱ ርኵስ አይደለምና፤ ምክንያቱም ሥጋ የተፈጠረው በራሱ በእግዚአብሔር ነው፡፡ አምላካችን ደግሞ ርኵስ ነገር አይፈጥርም፡፡ ሰውን (ሰው የነፍስና የሥጋ ተዋሕዶ ውጤት ነው) ከፈጠረ በኋላ ‹‹ያደረገውን ሁሉ አየ እነሆም እጅግ መልካም ነበረ፡፡›› ተብሏል፡፡ (ዘፍ1፥31) ሥጋ ርኵስ ቢሆን ኖሮ እግዚአብሔር ወልድ (ቃል) ‹‹ሥጋ ሆነ›› ባልተባለ ነበር፡፡ (ዮሐ 1፥14) አዳምና ሔዋን ከኃጢአት በንጽሕና ይኖሩ ነበር፡፡ ‹‹አዳምና ሚስቱ ሁለቱም ዕራቁታቸውን ነበሩ፣ አይተፋፈሩም ነበር›› እንዲል (ዘፍ 2፥25)  ህፃናት፣ ልጆች  ሰውነት አላቸው ነገር ግን የኃጢአት ምኞት የላቸውም፡፡
ስለዚህ ፈቃደ ሥጋን መዋጋት ማለት ሥጋን ማጥፋት ወይም ደግሞ ተፈጥሮአዊና ንጹህ የሆነ የሥጋን ፈቃድ ማስወገድ ማለት ሳይሆን፣ ኃጢአትን በማየት፣ በመስማት፣  በመለማመድ ያደገውን÷ ወደ ኃጢአት ያዘነበለውን ፈቃዳችንን መጐሰም/መግራት ማለት ነው፡፡ ይህ ፈቃድ (ኃጢአት) ሥጋን በመጠቀም ይሠራል÷ ሥጋን ከነፍስ ቁጥጥር ውጭ እንዲሆን ያደርገዋል፡፡
የሰው ሥጋዊ ባሕርዩ ምግብ ሲያጣ ይራባል፣ ይደክማል፣ ሥራ መሥራት ይሳነዋል፡፡ ሲሰጡት ደግሞ ኃጢአትን ተለማምዷልና ሌላ ፈቃድ በማምጣት ጠላት ሆኖ ይፈትነዋል፡፡ ‹‹ያዕቆብ በላ፣ ጠገበ፣ ወፈረ፣ ደነደነ፣ ሰባ፣ የፈጠረውንም እግዚአብሔርን ተወ፣ የመድኃኒቱንም አምላክ ናቀ፡፡ (ዘዳ 32፥15)
ሰውነት የሚፈልገውን ሁሉ እንደ ልቡ ካገኘና ያለ ገደብ የሚቀለብ ከሆነ ወደ ኃጢአት ለመገስገስ የተዘጋጀ መርከብ ነው፡፡ ሰውነት በተመቸውና ፈቃዱን ለመፈጸም ኃይል ባገኘ ጊዜ ነፍስ እየደከመች ትሄዳለች፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ሰውነት ፈጽሞ ከደከመና ከዛለ ሥራ መሥራት ያስቸግራል፡፡ ስለዚህ ሐዋርያው ‹‹ሰውነቴን እየጎሰምሁ አስገዛዋለሁ›› እንዳለ፡፡ በአግባቡ ሊያዝና ሊገራ ይገባዋል፡፡ (1ኛ ቆሮ 9፥27) በአጠቃላይ ቅዱስ ጳውሎስ ‹‹ወንድሞች ሆይ ዕዳ አለብን እንደ ሥጋ ፈቃድ ግን እንኖር ዘንድ ለሥጋ አይደለም፡፡ እንደ ሥጋ ፈቃድ ብትኖሩ ትሞቱ ዘንድ አላችሁና፤ በመንፈስ ግን የሰውነትን ሥራ ብትገድሉ በሕይወት ትኖራላችሁ›› እንዳለ ከፈቃደ ሥጋ ጋር በመጋደል ፈቃደ ሥጋችንን ለፈቃደ ነፍስ ማስገዛት ይገባናል፡፡
   ለ. ከርኵሳን መናፍስት ጋር የሚደረግ ጦርነት ነው፡፡
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ‹‹መጋደላችን ከደምና ከሥጋ ጋር አይደለምና ከአለቆችና ከሥልጣናት ጋር ከዚህም ከጨለማ ዓለም ገዦች ጋር እንጂ›› እንዳለ መንፈሳዊ ተጋድሎ ማለት ሰው ከሰው ጋር በመጣላት የሚያደርገው ትግል ሳይሆን ጥንተ ጠላታችን ከተባለው በእባብ ወይም በዘንዶ ከተመሰለው ዲያብሎስና ከእርሱ ጋር ካሉት ሠራዊቱና መልእክተኞቹ ጋር የሚደረግ ጦርነት ነው፡፡ (ኤፌ 6፥12)
ከአዳምና ከሔዋን ከልጃቸውም ከቃየን ጀምሮ ሰይጣን የሰው ልጆችን ዘወትር ይዋጋል፤ ከዘላለም የሞት ፍርድ ሥር ሊጥል ይሠራል፡፡ በዚህም ውጊያው ከነቢያት ፤ከሐዋርያት ፤ የእግዚአብሔር መንፈስ ካደረባቸው ሰዎች እንኳ ሳይቀር ብዙዎችን ጥሏል፡፡
ዛሬም በገዛ ባሕርያችን የሚገኘውን ፈቃደ ሥጋ በመጠቀም፣ የራሱን በመጨመርና የተለያዩ ፈተናዎችን በማቀናበር ይዋጋናል፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ ‹‹ባላጋራችሁ ዲያብሎስ የሚውጠውን ፈልጎ እንደሚያገሣ አንበሳ ይዞራልና›› በዓለም ያሉት ወንድሞቻችሁ ያን መከራ በሙሉ እንዲቀበሉ እያወቃችሁ በእምነት ጸንታችሁ ተቃወሙት፡፡›› እንዳለ ጠላት ዲያብሎስ ክርስቲያኖችን በኃጢአትና ሞት ሊውጥ ዘወትር ይተጋል፡፡ ማንም ሰው ደግሞ ከዚህ ፈተናና ውጊያ ሊያመልጥ አይችልም፤ ስለዚህ ሐዋርያት ‹‹በእምነት ጸንታችሁ ተቃወሙት››፣ ‹‹የዲያብሎስን ሽንገላ ትቃወሙ ዘንድ እንዲቻላችሁ የእግዚአብሔርን ዕቃ ጦር ሁሉ ልበሱ፡፡›› እንዳሉን የእግዚአብሔርን ዕቃ ጦር ሁሉ ለብሰን ልንዋጋው ይገባል፡፡ (1ኛ ጴጥ 5፥8-9፣ኤፌ 6፥11)
ሐ. የሚመጣውን ዓለም ደስታ ተስፋ እያደረጉ ብቻ በዚህ ዓለም ሕይወት ከደስታ ውጪ መሆን ማለት አይደለም፡፡
ደስታ በራሷ የቤተ ክርስቲያን መገለጫ የሆነች፤ ከእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ የተሰጠች፤ ንጹሕ ፈርጥ ነች፡፡ (ገላ 5፥22)
እውነት ነው፤ በዚህ ዓለም ስንኖር መከራ አለብን፡፡ ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መስቀሉን ተሸክመን እንድንከተለው አዞናል፡፡ እያንዳንዱ ክርስቲያን በዚህ ምድር ላይ እስካለ ድረስ ከጨለማው ዓለም ገዢ ከዲያብሎስና ከሠራዊቱ የሚመጣ ልዩ ልዩ ፈተናና ከሥጋችንም ባሕርይ ከሚገኘው ክፉ ምኞትና ርኵሰት ሥራ እንዲሁም ከሌሎቹ የኃጢአትና የፈተና ዓይነቶች ጋር በማያቋርጥ እልህ አስጨራሽ በሆነ ትግል ውስጥ መኖሩ የግድ ነው፡፡ መከራና ስቃይ፣ ትግልና ጦርነት የሌለበት በዘለዓለማዊ ደስታ ብቻ የሚኖርበት ሕይወት በሚመጣው ዓለም የሚገኝ ነው፡፡
በዚህ ምድር በጉዞ ላይ ያለችው ቤተ ክርስቲያን ጉዞዋን ጨርሳ ድል ከነሱት አባላቷ ጋር አንድ እስክትሆን ድረስ መከራው፣ እንቅፋቱ፣ መሰደዱ፣ መራቡ፣ መጠማቱ የግድ ነው፡፡ ‹‹ወደ እግዚአብሔር መንግሥት በብዙ መከራ እንገባ ዘንድ ያስፈልገናል፡፡›› እንዲል (ሐዋ 14፥22)
ይህ ሲባል ግን በዚህ ዓለም የሚኖሩ ክርስቲያኖች ከደስታ የተራቆቱ ዘወትር በኅዘንና በስቃይ ብቻ የሚኖሩ ናቸው ማለት አይደለም፡፡ ክርስቲያኖች የሚለዩትና ዘወትር ለመለየት ጥረት የሚያደርጉት የውሸት ከሆነው ኃጢአት (ዝሙት፣ ርኩሰት፣ መዳራት፣ ጣዖትን ማምለክ፣ ምዋርት፣ ጥል፣ ክርክር፣ ቅንአት፣ ቁጣ፣ አድመኝነት፣ መለየት፣ መናፍቅነት፣ ምቀኝነት፣ መግደል፣ ስካር፣ ዘፋኝነት፣ ይህንም የሚመስል) ከሚገኘው ደስታ እንጂ ከእውነተኛውና ከሰማያዊው ደስታ አይደለም፡፡
መንፈሳዊ ተጋድሎ በመንፈስ ቅዱስ አነሳሽነትና ረድኤት መንፈስ ቅዱስ መሪና አስተማሪ፣ የሚያነቃቃና የሚያጽናና፣ የሚያርምና የሚገሥጽ፣ የሚረዳና የሚያጸና፣ በመሆን ስለ ክርስቶስ በክርስቶስ ጸጋ የሚከናወን በመሆኑ መከራንና ስቃይን በሚያስረሳ እውነተኛ ደስታና ሰላም የተሞላ ሕይወት ነው፡፡
ቅዱስ ጳውሎስና ቅዱስ ሲላስ ስለ ክርስቶስ በማስተማራቸው ምክንያት ገዢዎች ልብሳቸውን ገፈው በበትር እንዲመቱ አዘዙ በበትር ከመቷቸውም በኋላ በወኅኒ ቤት ጣሏቸው እነርሱ ግን ከጀርባቸው ደም እየፈሰሰ በመንፈቀ ሌሊት እንኳን እግዚአብሔርን በመዝሙር ያመሰግኑ ነበር፡፡ እውነተኛውና ሰማያዊው ደስታ በልቡናቸው ሞልቶ ነበርና፡፡ (ሐዋ 16፥22-25)
መጽሐፍ ቅዱስ ስለ ሐዋርያት እንዲህ ይለናል ‹‹ ሐዋርያትንም ወደ እነርሱ ጠርተው ገረፏቸው  በኢየሱስም ስም እንዳይናገሩ አዝዘው ፈቷቸው፡፡ እነርሱም ስለ ስሙ ይናቁ ዘንድ የተገባቸው ሆነው ስለተቆጠሩ ከሸንጎው ፊት ደስ እያላቸው ወጡ፡፡››(ሐዋ 5፥40-41)
ቅዱስ ዮሐንስ ካሲያን የተባለው አባት በተጋድሎ በግብጽ በረሃ ውስጥ ይኖሩ ስለነበሩት መነኰሳት ሲናገር ‹‹ እነዚህ ምድራዊ መላእክት ናቸው፤ የግብጽን በረሀዎች በደስታ ወደ ተሞላ መዝሙርና እግዚአብሔርን የማመስገኛ ገነትነት ለውጠዋልና››  ብሏል፡፡
በአጠቃላይ መንፈሳዊ ተጋድሎ ማለት ከተድላ ሥጋ፣ በኃጢአት ከሚገኝ ደስታ በመሸሽ ሰማያዊና እውነተኘ በሆነ ሰላምና ደስታ ውስጥ መኖር ይህንንም ለማግኘት መጋደል ማለት ነው፡፡
       መንፈሳዊ ተጋድሎ ዓላማው ምንድነው?
ሀ. የድል አክሊል (የዘለዓለም ሕይወት) ለመቀበል
እግዚአብሔር አምላካችን ሰዎች ነፃ ፈቃዳቸውን ተጠቅመው ከአምላካቸው ጋር መኖር ከመረጡ ሊሰጣቸው ያዘጋጀው ከመነገርና ከመታሰብ በላይ የሆነ የዘለዓለም  ሕይወት አለ፡፡ የሰው ልጅ ሕሊናዊ ነፃ ፈቃዱ ደግሞ ከአዳምና ከሔዋን ውድቀት በኋላ በየጊዜው እየደከመና ወደ ኃጢአት እያዘነበለ መጥቷል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ የሰው ልጅ በእግዚአብሔር ዘንድ ከብሮ ባየ ጊዜ ከአባቶቻችን ጀምሮ ዘወትር የሚቀና ክፉ ጠላትም (ዲያብሎስ) አለን፤ ባገኘው አጋጣሚ ስንፍናችንንና ድካማችንን እየተከተለ እነዚህንም በመጠቀም ዘወትር ከአምላካችን ሊለየን እንደሚተጋም ከላይ ተመልክተናል፡፡

ሽልማት፣ አክሊል የሚሰጠው ደግሞ ማሸነፍ ለሚችል ጎበዝ ሰው ነው፡፡ ሰነፍና ቸልተኛ ሰው ግን ሊሸለም አይገባውም አንድ ሰው ጎበዝ ወይም ሰነፍ መሆኑ የሚታወቀው ደግሞ በፊቱ ያጋጠመውን ውድድር ወይም ፈተናና መከራ ማሸነፍና ማለፍ ሲችል ብቻ ነው፡፡

ስለዚህ የመንፈሳዊ ተጋድሎ ዓላማ በገዛ ባሕርያችን ያለን መጥፎ የኃጢአት ዝንባሌና ጠላታችን ዲያብሎስ የሚያመጣብንን ፈተናና ሽንገላ ከእግዚአብሔር ርዳታና ቸርነት ጋር ሕሊናን በማንቃት፣ ራስን በመግዛትና ጠንክሮ በመጋደል አምላካችን ያዘጋጀልንን የድል አክሊል የዘላለም ሕይወትን መቀበል ነው፡፡ ‹‹ የተጠራህለትን የዘለዓለም ሕይወት ትቀበል ዘንድ መልካሙን የሃይማኖት ገድል ተጋደል›› አንዲል (1ኛ ጢሞ 6፥12) ሐዋርያቅ ቅዱስ ጳውሎስ ብዙ መከራዎችን አልፎ ገድሉን በድል አድራጊነት ሲፈጽም ‹‹ መልካሙን ገድል ተጋድያለሁ፤ ሩጫዬን ጨርሻለሁ፤ ሃይማኖቴንም ጠብቄያለሁ፤ ወደ ፊት የጽድቅ አክሊል ተዘጋጅቶልኛል፤ ይህም ጻድቅ ፈራጅ የሆነው ጌታ ያን ቀን ለእኔ ያስረክባል፤ ደግሞም መገለጡን ለሚወዱ ሁሉ እንጂ ለእኔ ብቻ አይደለም፡፡›› ብሏል ( 2ኛ ጢሞ 4፥7-8)
ለ. ለመንፈሳዊ እድገት
ክርስቲያናዊ ሕይወታችን ለፍሬ የሚበቃው የድል አክሊልን መቀዳጀት የምንችለው የማያቋርጥ (የማይቆም) መንፈሳዊ ዕድገት ሲኖረን ነው፡፡ በጥምቀት ያገኘነው አዲሱ ሕይወታችን ዘወትር ማደግ ይኖርበታል፡፡ ክርስቲያናዊ ሕይወታችን በዛፍ ተክል ይመሰላል፡፡ ከችግኝ ማፍላት ጀምሮ ፍሬ እስከሚያፈራለት ጊዜ ድረስ ያለው ድካም ቀላል አይደለም፡፡ የዛፉ ችግኝ እንዲያበቅል፣ እንዲለመልም፣ አንዲያብብና እንዲያፈራ አትክልተኛው ያልተቆጠበ ጥረት ማድረግ ይኖርበታል፤ በየጊዜው ውሃ ማጠጣት፣ ማረምና መኰትኰት፣ ፀረ ዕፅዋትና ፀረ ሕይወት የሆኑ በሽታዎችን መከላከል ያስፈልጋል፡፡ እንደዚሁ ክርስቲያናዊ ሕይወታችን አድጎ ለፍሬ እስኪበቃ ድረስ ዕለተ ዕለት ጠንክረን በትዕግሥት መሥራት በመንፈሳዊ ተጋድሎ መጽናት ይገባል፡፡ የመንፈሳዊ ተጋድሎም ዓላማው መንፈሳዊ ሕይወታችንን የሚያቀጭጩ  ከጸጋ እግዚአብሔርም የሚያራቁቱ ኃጢአትና የዲያብሎስ ፈተናን በመቃወም መንፈሳዊ ምግቦችንም በመመገብ አዲሱ ሕይወታችንን ማሳደግ ነው፡፡
 ወስብሐት ለእግዚአብሔር ለዘበቅዱሳኒሁ ይሴባሕ ይእዜኒ ወዘልፈኒ ወለዓለም ዓለም አሜን፡፡ ወአሜን ለይኩን ለይኩን፡፡

Thursday, May 9, 2013

አቡነ ቀውስጦስ

   
      በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን ::

እንኳን ታላቁ ኢትዮጵያዊው አባት አቡነ ቀውስጦስ በዓለ ልደት አደረሳችሁ
በቤተክርስቲያናችን ግንቦት 1 ታስበው ከሚውሉ ታላላቅ አባቶች መካከል ኢትዮጵያዊው አባት አቡነ ቀውስጦስ አንዱ ናቸው፡፡ ለመሆኑ አቡነ ቀውስጦስ ማን ናቸው? ምንስ ቃል ኪዳን ተሰጣቸው? ባጭሩ እንመልከት ምልጃና በረከታቸው ይደርብን አሜን
ጻድቀ አባታችን አቡነ ቀውስጦስ የተወለዱት በሸዋ ክፍለ ሀገር በወግዳና ቡልጋ ውስጥ ሲሆን አባታቸው ገላውዲዮስ እናታቸው እምጽዮን ይባላሉ፡፡ የጻድቁ የአቡነ ተክለሃይማት እናት እግዚአኃሪያ እና እምነጽዮን ታናሽና ታላቅ እህትማማቾች ናቸው፡፡ ገላውዴዎሰ እና እምነጽዮን እግዚአብሔር የተባረከ ልጅ ይሰጣቸው ዘንድ ለዓመታት በእመቤታችን በቅድስት ድንግል ማርያም ስዕል ፊት ሲጸልዩና ሲለምኑ የእመቤታችንም ስዕል አፍ አውጥቶ አናገረቻቸው እንዲህም አለቻቸው፡፡ ‹‹አንድ ልጅ አስቀድማችሁ ትወልዳላችሁ የሚወለደውም እኔ በተወለድኩበት ግንቦት 1 ቀን ሲሆን እረፍቱም በእኔ የእረፍት ቀን ጥር 21 ነው፡፡ እሱም የሰማያዊ ንጉስ ጭፍራ ይሆናል፡፡ ››አለቻቸው በተገባላቸው ቃል መሰረት ግንቦት 1 ቀን ጻድቁ አቡነ ቀውስጦስ ተወለዱ፡፡
ጻድቁ አባታችን አቡነ ቀውስጦስ የዚህን ዓለም ተድላ ደስታና ጣዕም ንቀው ፈለገ ሐዋርያትን ተከትለው በሸዋ፤ በከፋና፤ በጅማ ዞረው የጌታችን የመድሐኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ወንጌል በማስተማር ከአረማውያን ነገስታትና ባላባቶች የሚደርስባቸውን መከራና እንግልት በመታገስ በተጋድሎ ጸንተው ብዙውን ሕዝብ ከአምልኮት ጣዖት ወደ አምልኮተ እግዚአብሔር ከኃጢያት ወደ ጽድቅ መልሰዋል፡፡በተለይ በሸዋ ክፍለ ሀገር ፈንታሌ ተራራ ላይ ሠረቲ ለምትባል ጠንቋይ እየተላላኩ ህዝቡን የሚያስቱና የሚያሰቃዩ አራት መቶ ሰባ ሺህ ሦስት መቶ አጋንንትን እንደ ነብዩ ኤልያስ በጸሎታቸው ከሰማይ እሳት አውርደው ተራራውን ደምስሰው አጋንንቱን አቃጥለዋል፡፡ሕዝቡንም ለጣዖትና ለጠንቋይ ከመገዛት አድነውታል፡፡
ጻድቁ አባታችን አቡነ ቀውስጦስ በብዙ ተጋድሎ ሲኖሩ በሰማዕትነት ያርፍ ዘንድ ስለ እግዚአብሔር መንግስትና ዘለዓለማዊ ሕይወት የሚተጉ እንጂ የዚህን ዓለም መንግሰት ሀብትና ሥልጣን የማይሹ እውነተኛ መናኝ ነበሩና የታናሽ ወንድማቸው የአጼ ይኩኖ አምላክ ልጅ አጼ አምደጽዮን የአባቱን እቁባት በማፈግባቱ ‹‹ይህንን ልታደርግ አይገባም››ብለው እንደ ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ (ማር 7፡14-29) ቢገስጹት 11 አሽከሮችን በሌሊት ልኮ ከበዮ ወደ እንሳሮ ሀገር ካስወሰዳቸው በኃላ ኮሶ አረህ ከሚባለው አፋፍ ላይ እኩለ ሌሊት በጦር ጎናቸውን አስወግቶ ደማቸውን አፈሰሰሰ፡፡ደማቸውም እስከታላቁ ወንዝ ጅማ ድረስ ሆነ፡፡የፈሰሰው ደማቸውም ቀይ ብርሃን ሲሆን የሌሊቱ ጨለማ ከጸሐይ ሰባት እጅ የሚበልጥ ብርሃን በአውራጃውቹ ሁሉ ታየ፡፡በዚህ የተነሳ እስከ ዛሬ ድረስ ሀገሩ ቀን ተብሎ ይጠራል፡፡
በብዙ ተጋድሎ ከቆዩ በኃላ ነፍሳቸው ከሥጋቸው ሳትለይ በስቃይ ላይ ላሉም በዘመናቸው ሁሉ ስለነበራቸው ተጋድሎ ንጽህናና ምናኔ ጌታችን መድሐኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እናቱ ድንግል ማርያምና ቅዱሳኑኑ እና መልአክታኑን አስከትሎ ቃል ኪዳን ሊሰጣቸው መጣ፡፡ እንዲህም አላቸው እኔ ለአንተ ዓይን ያላውን ጆሮ ያልሰማውን መንግስተ ሰማያትን አዘጋጀውልህ በዚያም ታላቅ ወንበር ታገኛለን በዘመንህ ስላሳለፍካቸው ክርስቲያናዊ ተጋድሎህ 7 የብርሃን አክሊላትን አዘጋጀውልህ 2ቱ እንደ እነ ነብዩ ኤልያስና ነብዩ ሳሙኤል ለሆነ ንጽህናህ 2ቱ እንደ እነ ቅዱስ ጴጥሮስና ቅዱስ ጳውሎስ ለሆነ የወንጌል ስብከትህ 2ቱእንደ እነ ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ቅዱስ ፊቅጦር በትዕግስት ሥለተጋደልክ አንዱ ስለ ልብ ርህራሄ ነው አላቸው፡፡
እንዲሁም ስለ እኔ ምስክርነት የሞትክባት ምድር እንደ ዳዊት ሀገር እንደ ኢየሩሳሌም ትሁንልህ ወደ እርሷ የሄደውንም ሁሉ ወደ ኢየሩሳሌም ወደ መቃብሬ ጎሎጎታ እንደ ሄደ እቆጥርለታለሁ፡፡ ብዙ ኃጢያት የሰራ ሰው ንሰሐ ገብቶ በዚህች ሀገር በስምህ ጥቂት ምጽዋት ቢሰጥ እኔ ኃጢያቱን እደመስስለታለሁ፡፡በጠበልህም ቢጠመቅ በደሉን አጠፋለታለሁ፡፡ደምህ በምድሪቷ ፈሷልና፡፡
በእረፍት ዕለትህ ለቤተክርስቲያን ለቅዱስ ቁርባን ስንዴ ወይንና ዕጣን ያቀረበ ኃጢያት የሰራ ቢሆን ንሰሐ ቢገባ ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን እንደተቀበለ ንጹህ ሰው አደርገዋለው፡፡ ለስምህ መታሰቢያ በታነጸው ቤተ መቅደስ በንጹህና ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን የሚቀበል ሰው ራሱን ቤተሰቡን እና ባልጀሮቹን ያድናል፡፡
ጌታችን መድሐኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለጻድቁ አባታችን አቡነ ቀውስጦስ ይህንን ቃል ኪዳን ሰጥቷቸው ወደ ሰማይ አረገ፡፡ቅዱሳን መልአክትም ነፍሳቸውን ከሥጋቸው በክብር ለዩ፡፡ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም በሰማይ መካከል ሆና ነፍሳቸውን በፈገግታ ተቀበለች ፡፡
የእረፍታቸውም እለት እመቤታችን ባረፈችበት ጥር 21 ቀን በመሆኑ እመቤታችንም መታሰቢያህን ለሚያደርጉ ሁሉ በልጄ በረከት እባርካቸዋለሁ ብላ ቃል ኪዳን ገባችላቸው፡፡ ጻድቁ አባታችን አቡነ ቀውስጦስ ባረፉበት ዕለትም ብዙዎች ከደዌአቸው በረከትና ፈውስ አግኝተዋል፡፡ አሁንም ድረስ ደማቸው በፈሰሰበትና አጽማቸው ባረፈበት ቦታ ብዙ ምዕመናን ፈውሰ ሥጋ ፈውሰ ነፍስ እያገኙበት ነው፡፡የጻድቁ አባታችን አቡነ ቀውስጦስ በዓል ግንቦት 1 ቀን የተወለዱበት ጥር 21 ቀን ያረፉበትና ቃል ኪዳን የተቀበሉበትን በማዘከር በታላቅ ድምቀት በገዳሙ ይከበራሉ፡፡
ገዳመ ቀውስጦስ የሚገኘው ከአዲስ አባባ በስተሰሜን 120 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ሲሆን ወደ ደብረ ሊባኖስ በሚወስደው መንገድ ሙከጡሪ ከተማ ሲደርሱ ወደ ቀኝ በመታጠፍ ሚቴና በዩ በሚባለው አካባቢ ልዩ ስሙ መገንጠያ ከሚባል ቦታ ነው ውይም ወደ ጅሩ አርሴማ ቅድስት ሲሄዱ ወርደው ከአቡነ ቀውስጦስ ተባርከው መሄድ ይችላሉ ፡፡መንገዱ እዚያው ገዳሙ ድረስ መኪና የሚያስገባ በመሆኑ ምዕመናን ቦታው ድረስ በመሄድ ከጻድቁ አቡነ ቀውስጦስ በረከት ማግኘት የምትችሉ መሆኑን እገልጻለን፡፡የጻድቁ አቡነ ቀውስጦስ ረድኤትና በረከት ጸሎት ዘወትር አይለየን አሜን ፡፡ አባት ሆይ በረከትህን እናገኝ ዘንድ ባርከን!!!
ምንጭ፡-ገድለ አቡነ ቀውስጦስ

ጸሀፊ ገዛኸኝ ፈንታሁን

Saturday, April 27, 2013

ሆሣዕና


የዓብይ ጾም  ስምንተኛ ሳምንት ሆሣዕና
በዚህ ዕለት አይሁድ ጌታ ወደ ኢየሩሳሌም እንደሚመጣ በሰሙ ጊዜ የዘንባባ ዝንጣፊ ይዘው ሊቀበሉት ወጥተዋል፡፡ /ዮሐ.12÷12/ ዘንባባ የድል ማብሠሪያ ምልክት ነው፡፡ ጌታ የጨለማውን ኃይል በሞቱ ድል የሚነሣ ነው፡፡ የድል አድራጊነት ዘንባባ የተገባው ለዚህ ነው፡፡ የደስታችን ምንጩ ደስታን ለሚሰጥ ለእርሱ የደስታ መግለጫ ዘንባባ ቀረበለት፡፡ ሰላምን ደስታን ለዓለም ሁሉ የሚያድል ሰማያዊ ንጉሥ ክርስቶስ ነው፡፡ ከሞትና ከመበስበስ ጠብቆ ዘለዓለማዊውን ደስታ ያደለ ክርስቶስ፡፡

በዚህ የነበሩትም /መዝ.117÷25/ ያለውን የትንቢት ቃል እየዘመሩ ጮሁ፡፡ ይህም ይመጣል የተባለውን መሲህ እንዴት በጉጉት እየጠበቁት እንደነበር የሚያስረግጥ ነው፡፡ ክብር እንደሚሻ ደሀ ና የተዋረደ ሆኖ ቢመጣም እንደ ንጉሥ እና የእስራኤል አዳኝ ተቀበሉት፡፡ እንደ የጽድቅ ንጉሥ ተቀበሉት፡፡ ሆሣዕና አያሉም ጮኹ፡፡ ክርስቶስ መድኃኒት የሆነ ንጉሥ ነው፡፡ የጎሰቆለውን የሰውን ሰውነት የሚያድን የአርያም መድኃኒት፡፡ በዚህም በመዝሙራቸው ከዳዊት ጋር ተባበሩ፡፡ /መዝ.23÷7/

“በጌታ ስም የሚመጣ የእስራኤል ንጉሥ የተባረከ ነው” ጌታ ነውና በራሱ ስም መጣ፡፡ /ዮሐ.1÷1/ እስራኤል የንጉሣቸውን መምጣት በተንሸዋረረ መንገድ ይጠብቁት ስለነበር መምህራነ አይሁድ አልወደዱትም፡፡

ክርስቶስ የእስራኤል ንጉሥ መሆን ምን የሚረባው ሆኖ ነው? ክርስቶስ የእስራኤል ንጉሥ በመሆን ግብር የሚሰበስብ ወታደር በማደራጀት ጠላቶቹ ላይ ጦርነት የሚያውጅ አይደለም፡፡ ቢያምኑበት ቢታዘዙት የልቦናቸው ንጉሥ ሊሆን መጥቷል፡፡ እምነት ተስፋ ፍቅርን ገንዘብ ቢያደርጉ የሰማያዊ መንግሥቱ ዜጎች ሊያደርጋቸው የጽድቅ ንጉሥ ሆኖ መጣ፡፡ ሐሰትን በመናገር ሳይሆን ጽድቅን /እውነትን/ በመስበክ የነገሠ ንጉሥ ነው፡፡ ወልደ እግዚአብሔር ዓለም በእርሱ ቃልነት የተፈጠረ የዓለም ሁሉ ንጉሥ በፈቃዱ የእስራኤል ንጉሥ ተባለ፡፡ በምድር የእስራአል ንጉሥ የተባለ ክርስቶስ በሰማያትም የመላአክት ንጉሥ ነው፡፡ “አንቺ የጽዮን ልጅ ሆይ÷ አትፍሪ፤ እነሆ÷ ንጉሥሽ በአህያ ውርንጫ ላይ ተቀምጦ ይመጣል” /ዮሐ.12÷15/ ጌታ ብዙ ጊዜ ከቦታ ቦታ ሲዘዋወር የተጓዘው በእግሩ ነው፡፡ አሁን ግን አስደናቂ በሆነ ሁኔታ በአህያ ውርንጫ ተቀምጦ ወደ ኢየሩሳሌም ገባ፡፡ ትሑት ንጉሥ ኢየሱሱ ክርስቶስ፡፡ ንጉሥ ተብሎ ወደሚከብርበት ቦታ ሲያመራ አምሮ÷ ተውቦ በአማረ ልብስ÷ በአማረ መጓጓዣ የማይሄድ ትሑት ንጉሥ ክርስቶስ በአህያ መቀመጡ ብቻ ሳይሆን አህያይቱ እንደ ሰሎሞን አህያ በተዋቡ ቁሳቁስ ያጌጠች አልነበረችም፡፡ /መኃ.መኃ.3÷9/ የክርስቶስ ክብር በቁሳዊ ነገር የሚገለጥ አይደለም፡፡ መንግሥቱ ሰማያዊ እንጂ ምድራዊ አይደለምና በምድራዊያን ነገሥታት የንግሥና ወግ ልብስና ጌጥ አልመጣም፡፡ እጅግ ትሑት ንጉሥ አምላካችን ክርስቶስ ነው፡፡ ነቢዩ የጽዮን ልጅ እንድትነሣ ልቦናዋን በድል አድራጊነት ደስታ የሚሞላትን ንጉሥ እንድትቀበል ያዛታል ስለዚህ ፈፅማ እንድትደሰት ጠየቃት፡፡ ፍርሃቷንና ሀዘኗን የሚያጠፋ ንጉሥ መጥቷልና፡፡ የነቢዩ ዘካርያስ ትንቢት በዚህ ፍፃሜውን አገኘ፡፡ /ዘካ.9÷9/ ክርስቶስ ከሮማውያን ወይም አይሁዳውያን ጠላት የሆኑትን ሊበቀል የመጣ አይደለም፡፡ ሰማያዊ ሰላምና ክብር ሊያጎናፅፋቸው እንጂ፡፡ ይህንን ቅዱስ ሉቃስ “በሰማይ ሰላም በአርያምም ክብር” በማለት የገለጠው ነው፡፡ /ሉቃ.19÷38/ ጠላቶቹን እስከ መስቀል ሞት የወደደ የፍቅር ንጉሥ በመግደል ሳይሆን በመሞት በልቦናችን የነገሠ የፍቅር ንጉሥ ክርስቶስ ነው፡፡ “አትፈሪ” የሚመጣው የሚያከብራት ነውና ፍርሃትን እንድታስወግድ ተበሰረች፡፡ እርሱ መከራዋን ለመቀበል ደሙን በማፍሰስ ኃጢአትን ሊደመስስ ሕይወትን ሊሰጣት መጥቷልና አትፍሪ ተባለች ቤተ አይሁድ፡፡ ውርንጫይቱ ቀድሞ ምንም ጭነት የማያውቃቸው ሕግን ያልተቀበሉ በሕግ ያልኖሩ አሕዛብ ምሳሌ፤ አህያይቱ ጭነት የለመደች ሕግና ሥርዓት ተሰርቶላቸው የነበሩ የእስራአል ምሳሌ ናቸው፡፡ /ቅዱስ አውግስጢኖስ/“ የጽዮን ልጅ ሆይ አትፍሪ” አለ፡፡ ቀድመው አይሁድ ላይ ነግሠው የነበሩ ጨካኞች እና ኢፍትሐዊያን ስለ ነበሩ፡፡ ለጠላቶቻቸው አሳልፈው የሰጧቸው ነገሥታት ስለነበሩ፡፡ ክርስቶስ ግን የፍትሕ እና የርሕራሔ ንጉሥ ሆኖ መጥቷል፡፡ /ቅድስ ዮሐንስ አፈወርቅ/ “ደቀ መዛሙርቱ ግን ይህ ሁሉ ሲሆን አላስተዋሉም ነበር እስከ ጌታ ትንሣኤም በዚሁ ያለመረዳት ጉዞ ገፈተውበታል” /ዮሐ.12÷16/ ሐዋርያት በወቅቱ የተፈፀሙትን ተግባራት እውነተኛ ምሥጢራቸውን ለማስተዋል አለመብቃታቸውን ወንጌላዊ ነገረን፡፡ በወቅቱ ሐዋርያት በዙሪያቸው የሚፈጸሙ ተግባራት እውነተኛ ምንነታቸው እንደማይረዱ ሕፃናት ነበሩ፡፡ በኋላ በጌታ ስቅለት÷ ትንሣኤና እርገት በእውቀት እና በመንፈስ ቅዱስ በጎለመሱ ጊዜ በዕለተ ሆሣዕና የሆነውን ሁሉ ተረዱ፡፡ “ነገር ግን ጌታችን ከከበረ በኋላ በዚያን ጊዜ ይህ ሁሉ ስለ እርሱ እንደተፃፈ ይኸንም እንዳደረጉለት ትዝ አላቸው” ዮሐ.12÷17/ የእግዚአብሔርን ምሥጢር ለመረዳት ትንሣኤ ልቡና ያስፈልጋል፡፡ በዓለ ሆሣዕና ክርስቶስ የጽድቅ የትሕትና እና የድኅነት ንጉሥ እንደሆነ በአደባባይ የተገለጠበት ነው፡፡ ሕዝብና አሕዛብን አንድ ለማድረግ እንደመጣ በምሥጢር የገለጠበት ዕለት ነው፡፡ ሐዋርያት በጌታ ትንሣኤና እርገት ምሥጢር እንደተረዱ የፍቅር የትሕትና እና ድኅነት የሆነ የክርስቶስን ነገር በትንሣኤ ልቡና ተረድተን የሰማያዊ መንግሥቱ ዜጎች ለመሆን ያብቃን አሜን!

Thursday, April 18, 2013

ስለ ጸሎት

                                                                                   በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን::

“አንትሙሰ ሶበት ጸልዩ ስመ ዝበሉ፡፡” ማቴ.6፥
እናንተስ በምትጸልዩበት ጊዜ እንዲህ በላችሁ ጸልዩ “አባታችን ሆይ በሰማያት የምትኖር ስምህ ይቀደስ መንግሥትህ ትምጣ ፈቃድህ በሰማይ እንደሆነ እንዲሁ በምድር ይሁን….
በዚህ የጸሎት ክፍል ክብር ምስጋና ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከ81 መጻሕፍት የተገኙ አምስት ቁም ነገሮችን አስተምሯል፡፡
  1. ሃይማኖት
  2. ተስፋ
  3. ፍቅር
  4. ትሕትና
  5. ጸሎት
1.   ሃይማኖት፡- ሃይማኖት ማለት በዐይናችን ያላየነውን አምላክ አባታችን ሆይ ሲሉ መኖር ነው ቀደም ሲል የነበሩ አበው ነቢያት ሲጸልዩ እግዚእነ አምላክነ ንጉሥነ እያሉ ይጸልዩ ነበር፡፡ ይህም ከግብርናተ ዲያብሎስ /ለዲያብሎስ ከመገዛት/ እንዳልዳኑ ለማጠየቅ ነው፡፡ እኛን ግን ከግብርናተ ዲያብሎስ ነጻ አውጥቻችኋለሁ ሲል አባታችን ሆይ ብላችሁ ጸልዩ ብሎ አስተማረን፡፡ “ልጆች እንደመሆናችሁ መጠን እግዚአብሔር አባ አባቴ ብላችሁ የምትጠሩትን የልጁን መንፈስ በልባችሁ አሳደረ” /ገላ.4፥6፣ ሮሜ.8፥15/፡፡ አባትነቱንም በሁለት ነገር ከምድራዊ አባት ለይቶታል፡፡
በመውለድና በመግቦት ከምድራዊ አባት ይለያል፡፡ ምድራዊ አባት በዘር በሩካቤ ይወልዳል፡፡ በማር፣ በወተት፣ በፍትፍት ያሳድጋል፤ ኋላም በሞት ሲያልፍ የምታልፍ ርስትን ያወርሳል፡፡ እርሱ ግን ሲወልደን በርቀት ሲያሳድገንም በሥጋውና በደሙ ነው፡፡ “ከሥጋ የተወለደ ሥጋ ነው፥ ከመንፈስ የተወለደ መንፈስ ነው ዮሐ. 3፥6፡፡ ኋላም የማታልፍ ርስት መንግሥተ ሰማያትን “በክርስቶስ ደግሞ ርስትን ተቀበልን” ኤፌ.1፥11፣ 1ኛጴጥ.3፥5፡፡ በአበው ነቢያት ሐዋርያትን፣ በሐዋርያትም እኛን አቅርቦ አባታችን ሆይ ብለን እንድናመሰግነው አዞናል፡፡
ምድራዊ አባት የሚመግበው እግዚአብሔር ስለሚሰጠው ለልጁ በመስጠት ተቀብሎ በማቀበል ነው፡፡ እርሱ ግን መመገብ የባሕርዩ ስለሆነ ከሌላው ነስቶ አይደለም፡፡ ምድራዊ አባት ሲያጣ አጣሁ ይላል እርሱ ግን አያጣም፡፡ ምድራዊ አባት ሰጥቶ ሲያልቅ አለቀ ይላል፡፡ የእርሱ ግን ስጦታው አያልቅም፡፡ “በሰማያት የማያልቅ መዝገብ የሚሆኑትን የሚያረጁትን ኮረዶች ለራሳችሁ አድርጉ” ሉቃ.12፥33፡፡ ምድራዊ አባት ከትልቁ ልጁ ይልቅ ለትንሹ የደላል እርሱ ግን ዓለምን በእኩል ምግብና ይመግባል፡፡ ምድራዊ አባት ትዕዛዙን ካልተጠበቀለት ልጁን ከቤት ያስወጣል፣ ያባርረዋል እርሱ ግን ሁል ጊዜ በትዕግስት ይመለከተናልና፡፡ “በጻድቃንና ለኀጥአንም ዝናምን ያዘንማልና” ማቴ.5፥45፡፡  እኛ አባትነቱን አምነን አባታችን ሆይ ብንለው እኛ ልጆቹ መሆናችን የልጅነት ሥልጣን እንዳገኘን እንመሰክራለን፡፡ “ለተቀበሉት ሁሉ ግን በስሙ ለሚያምኑት ለእነርሱ የእግዚአብሔር ልጆች ይሆኑ ዘንድ ሥልጣንን ሰጣቸው፡፡ እነርሱም ከእግዚአብሔር ተወለዱ እንጂ ከደም ወይም ከሥጋ ፈቃድ ወይም ከወንድ ፈቃድ አልተወለዱም” እንዲል ዮሐ.1፥12፡፡ “የእግዚአብሔር ልጆች ተብለን ልንጠራ አብ እንዴት ያለውን ፍቅር እንደሰጠን እዩ 1ዮሐ.3፥1፡፡
ከላይ ያየናቸው የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች የሚያስረዱን የእግዚአብሔር ፍቅር ከምድራዊ አባት የተለየ መሆኑን ነው፡፡ ምድራዊ አባት ልጁን ቢወደውም ሥልጣን አይሰጠውም፡፡ እግዚአብሔር ግን ለልጆቹ አጋንንትን እንዲያወጡ ድውያንን እንዲፈውሱ ለምጽ እንዲያነጹ ሙታን እንዲያስነሡ ሥልጣን ሰጥቷል፡፡ “አሥራ ሁለቱን ደቀመዛሙርቱን ወደ እርሱ ጠርቶ እንዲያወጡአቸው በርኩሳን መናፍስት ላይ ደዌንና ሕማምንም ሁሉ እንዲፈውሱ ሥልጣን ሰጣቸው” እንዲል ማቴ.10፥1፡፡
በመኖሪያው /በሰማያት/ በመኖሩ ከምድራዊ አባት ይለያል፡፡ በሰማያት የምትኖር ብሎ በመኖሪያው ከምድራዊ አባት ለይቶታል፡፡ አሁን እግዚአብሔር በምድር የሌለ በሰማይ ብቻ የተወሰነ ሆኖ አይደለም በሰማይም በምድርም የመላ አምላክ ነው፡፡ “ከመንፈስ ወዴት እሔዳለሁ? ከፊትህስ ወዴት እሸሻለሁ? ወደ ሰማይ ብወጣ አንተ በዚያ ነህ ወደጥልቅም ብወርድ በዚያ አለህ፡፡ እንደንስር ክንፍን ብወስድ /ቢኖረኝ/ እስከባሕር መጨረሻም ብበርር በዚያ እጅህ ትመራኛለች፡፡” መዝ.139፥7 በማለት ቅዱስ ዳዊት እግዚአብሔር የሌለበት ቦታ እንደሌለ ገልጿል፡፡
በሰማያት የምትኖር በሉኝ ያለን ብዙ ጊዜ መገለጫው፣ መቀመጫው፣ ለቅዱሳን እርሱ በወደደ እነርሱ በሚችሉት መጠን የተገለጠና የታየ በሰማይ ስለሆነ ነው፡፡
“ንጉሡ ዖዝያን በሞተበት ዓመት እግዚአብሔርን በረጅምና ከፍ ባለ ዙፋን ላይ ተቀመጦ አየሁት የልብሱን ዘርፍ መቅደሱን መልቶት ነበር” ኢሳ.6፥1-6፡፡
“እግዚአብሔር እንዲህ ይላል ሰማይ ዙፋኔ ነው ምድርም የእግሬ መርገጫ ናት” ኢሳ.66፥1፡፡
ኢሳይያስ ምልአቱን፣ ክብሩን፣ ልዕልናውን በአየው መጠን ነገረን፡፡ ይህን የአገልጋዩ የኢሳይያስን ምስክርነት ሳይለውጥ ነቢያት የተናገሩልኝ የስተማሩልኝ፣ የሰበኩልኝ እኔ ነኝ በማለት እነ “ኢሳይያስ ሰማይ ዙፋኔ ነው” ያለውን እንደአስተማሩ እርሱም በሰማያት የምትኖር ብላችሁ አመስግኑኝ አለን፡፡ ስለ ልዕልናው ስለ ክብሩ በሰማይ አለ ይባላል፡፡ “በእንተ ዕበይከ ትትሜሰል በደመናት” እና ትርጓሜ ወንጌል “ስለ ልዕልናህ በደመናት ትመሰላለህ” ከዚህም የተነሣ ጌትችን ሲያስተምር “በሰማያ አትማሉ የእግዚአብሔር ዙፋን ነውና በምድርም አትማሉ የእግሩ መረገጫ ናትና” ማቴ.5፥32 ብሏል፡፡ ቅዱስ እስጢፋኖስ ጌቶችን ኢየሱስ ክርስቶስን በአየው ጊዜ እንዲህ መስክሯል “ወደሰማይ ትኩር ብሎ ሲመለከት የእግዚአብሔርን ክብር ኢየሱስንም በእግዚአብሔር ቀኝ ቆሞ አየና እነሆ ሰማያት ተከፍታው የሰው ልጅም በእግዚአብሔር ቀኝ ቆሞ አያለሁ አለ” ሐዋ.7፥55፡፡
ስለዚህ ብዙ ጊዜ በሰማይ ለወዳጆቹ ከመገለጡ የተነሣ አባታችን ሆይ በሰማያት የምትኖር ብላችሁ አመስግኑኝ አለን፡፡
2.    ተስፋ፡- ተስፋ ማለት የወደፊት አለኝታ እናገኘዋለን ብለን የምንጠብቀው መከራ የምንቀበልለት፣ በዚህ ዓለም ባይመቸን መከራ ቢጸናብን፣ ብንገፋ ብንከፋ ብናዝን ብንጨነቅ ያልፋል ብለን የምንጽናናበት ነው፡፡ ይህን ተስፋ ቅዱስ ጳውሎስ እንዲህ ብሎ ገልጾታል፡፡ “በእግዚአብሔር ክብርም ተስፋ እንመካለን፡፡ ይህም ብቻ አይደለም ነገር ግን መከራ ትዕግሥትን እንዲያደርግ ትዕግሥትም ፈተናን ፈተናም ተስፋን እንዲያደርግ እያወቅን በመከራችን ደግሞ እንመካለን፡፡ በተሰጠንም በመንፈስ ቅዱስ የእግዚአብሔር ፍቅር በልባችን ስለፈሰሰ ተስፋ አያሳፍርም” ሮሜ.5፥2-5 ተስፋ ከላይ ቅዱስ ጳውሎስ እንደነገረን ሰማዕታት ከነደደ እሳት ገብተው፤ የተሳለ ስዕለትን ታግሰው፤ የዓላውያን ነገሥታትን ግርማ አይተው ሳይደነግጡ፣ ሃይማኖታቸውን ሳይለውጡ፣ ሹመቱን ሽልማቱን ወርቁን ብሩን ምድራዊ ክብራቸውን ትተው መከራ የተቀበሉት ለተስፋ መንግሥተ ሰማያት ነው፡፡ ጻድቃንም ድምጸ አራዊትን ግርማ ሌሊትን ፍትወታት እኩያትን ታግሰው፣ በምናኔ በተባሕትዎ ከዘመድ ባዳ ከሀገር ምድረ በዳ ይሻለናል ብለው የኖሩት ለዚሁ ተስፋ ነው፡፡ ይህንንም ቅዱስ ጴጥሮስ በሃይማኖት ምክንየት ተበትነው ለነበሩ ምዕመናን ሲጽፍ እንዲህ ብሎአል፡፡ “እስመ በእንተ ዝንቱ ተጸዋእክሙ ከመ በረከተ ትረሱ በእንተ ዛቲ ተስፋክሙ” ለዚች ተስፋችሁ መከራን ትቀበሉ ዘንድ ተጠርታችኋልና 1ጴጥ.2፥22 የህ ተስፋ መጻሕፍት የተባበሩበት ነው” በተስፋ ያጽናናልና ነገር ግን ተስፋ የሚደረግበቱ ነገር ቢታይ ተስፋ አይደለም፡፡ የሚያየውንማ ማን ተስፋ ያደርገዋል? የማናየውን ግን ተስፋ ብናደርገው በትዕግስት እንጠባበቃለን” ሮሜ. 8፥24፡፡ ስለዚህ ተስፋ የምንለው የማናየውን መንግሥተ ሰማያትን ነው፡፡ ይህን ተስፋ በጸሎታችን ውስጥ መንግሥትህ ትምጣ ብለን እንድንለምን ጌታችን አስተማረን፡፡ አሁን መንግሥትህ ትምጣ ስንል መንግሥተ ሰማያት ክንፍ ኖሯት በራ፣ እግር ኖሯት ተሽከርክራ የምትመጣ ሆኖ አይደለም ትሰጠን በሉኝ ሲል ተስፋ የምናደርጋት መንግሥትን እንዲያወርሰን ለምኑ አለን፡፡
3.    ፍቅር ፡- ፍቅር ማለት አንዱ ለሌላው መጸለይ ነው፡፡ ይኸውም “የዕለት ምግባችንን ዛሬ ስጠን” የሚለው ነው፡፡ ሰው ሁሉ አባታችን ሆይ የሚለውን ጸሎት ሲጸልይ የዕለት እንጀራዬን ሰጠኝ ብሎ”  አይጸለይም ለጠላቶቹም ለወዳጆቹም ጠቅላላ ሰው ሆኖ የተፈጠረ የተፈጥሪሮ ወንድምና እኅት ሁሉ ነው፡፡ ምክንያቱም ለእገሌ የሚል አደለም፡፡ ጠቅል አድርጎ የዕለት ምግባችንን ስጠን የሚል ነውና፡፡ ይህ ፍቅር ነው ሊቃውንት በትርጓሜያቸው ይህን ሲተረጉሙት ዕለት ዕለት እንድንማር፣ ሥጋውን ደሙን እንድንቀበል፣ ንሰሓ እንድገባ አድርግ ማለት ነው ይላሉ፡፡ ከምግበ ሥጋ ያለፈ ጸሎት ነው፡፡ ይህም ጸሎት ለሕዝቡ ለአሕዛቡ ለጠላት ለወዳጅ ለዘመድ ለባዕድ ሳይባል ለሁሉም የሚጸለይ ጸሎት ሲሆን እግዚአብሔር እኛን እንደወደደን እርስ በእርሳችንም እንዋደድ ዘንድ ተዋደዱ “ጠላቶቻችሁንም ውደዱ ለሚያሳድዷችሁ ጸልዩ” ብሎ አስተምሮኗል፡፡  ለሁሉም የሚሆን የጸሎት ፍቅርን የሚገልጽ ጸሎት “የዕለት ምግባችንን ስጠን” በሉኝ አለን፡፡
4.    ትሕትና፡- ትሕትና ማለት ራስን ዝቅ ማድረግ ማዋረድ ከሁሉ በታች ማድረግ ትዕቢትን ኩራትን ትዝህረትን ማስወገድ ነው፡፡ “ትዕቢትን ግን አታስቡ ራሲን የሚያዋርደውን ሰው ምሰሉ ሮሜ.12፥16፡፡ ይህም “ኀጢአታችንን ይቅርበለን” የሚለው ነው ይህን ጸሎት የበቃውም ያልበቃውም ይጸልየዋል፡፡ የበቃው የነጻው ከኃጢአት አልፎ ከአስረኛው መዓርግ የደረሰው ሁሉ ይጸልየዋል፡፡ ይህንን ሲጸልይ ግን ራሱን ዝቅ አድርጎ ከእኛ መደብ ውስጥ አስገብቶ ኀጢአታችንን ይቅር በለን ይላል፡፡ እርሱ ግን ከኀጢአት አልፎአል ስለትሕትና እኛን መስሎ እንደኛ ሆኖ ይጸልየዋል፡፡ ጌታችን ብዙ ጊዜ ስለትሕትና አስተምሯል፣ “እንግዲህ እንደዚህ ሕፃን ራሱን የሚያዋርድ ሁሉ በመንግሥተ ሰማያት የሚበልጥ እርሱ ነው” ማቴ 18፥4 “ማንም ከእናንተ ታላቅ ሊሆን የሚወድ የእናንተ አገልጋይ ይሁን ከእናንተ ማንም ፊተኛ ሊሆን የሚወድ የእናንተ ባሪያ ይሁን” ማቴ 20፥26-28፡፡
“ራሱን ከፍ የሚያደርግ ሁሉ ይዋረዳል ራሱንም የሚያዋርድ ሁሉ ከፍ ይላል” ማቴ 23፣11 እነዚህና ጌታችን ያስተማራቸውን በተግባር የሚያውሉ ቅዱሳን በቅተው ሳለ እንዳልበቁ ራሳቸውን ዝቅ በማድረግ ይጸልያል፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ ከጌታው ከኢየሱስ ክርስቶስ እንደተማረው የትሕትና ጥቅምን ጽፎአል “እንግዲህ በጊዜው ከፍ እንዲያደርጋችሁ ከኀይለኛው ከእግዚአብሔር እጅ በታች ራሳችሁን አዋርዱ” 1ጴጥ 5፥6፡፡ በዚህ ጸሎት ውስጥ ይህ ጠቃሚ የሆነ ጸሎት ተአምኖ ኀጣውእ (ኀጢአትን ማመን) ያለበት በደላችንን ይቅር በለን የሚለው ትሕትና ነው፡፡
5.    ጸሎት ፡- ጸሎት አባታችን ሆይ ብሎ እስከ መጨረሻው ያለው ነው አባችን ሆይ ስምህ ይቀደስ መንግሥት ትምጣ ፈቃድ ይሁንልን ይደረግልን የዕለት እንጀራችንን ስጠን በደላችንን ይቅር በለን ጸሎት ነው ታዲያ ይህን በንባብ አጭር በምሥጢር ጌታ መጻሕፍት ያጠቃለለ ታላቅ ጸሎት አፍ ንባብ ይነዳ ልብ ጓዝ ያስናዳ እንዲሉ አበው ኅሊናን በማባከን ሳይሆን በንቃት፣ በትጋት ሆነን ብንጸልይ እንጠቀማለን፡፡ ስለዚህ ነው ክብር ምሥጋና ይግባውና አባታችን ሆይ ብላችሁ ጸልዩ ያለን፡፡
 “ስብሐት ለእግዚአብሔር ለዘአብጽሐና እስከ ዛቲ ሰዓት”
ወስብሔት ለእግዚአብሔር ወለ ወላዲቱ ድንግል ወለ መስቀሉ ክቡር አሜን::

Saturday, April 13, 2013

የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ተአምር

     በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን::
ይህ የእመቤታችንን ድንቅ ተአምር የተነገረው ነሃሴ 19/2003 በግቢ ገብርኤል ቤተክርስቲያን የማታ ጉባኤ ሲሆን ነገሩም እንዲህ ነው ፦ ተአምሩን የመሰከሩት አንዲት እናት ሲሆኑ “የእመቤቴን ስም እየጠራሁ ያለአባት ያሳደግኩት ልጅ ነበርኝ ፡ እኔም ልጄም እመቤታችንን በጣም እንወድ ነበረ ፡ ያለአባት በእመቤቴ ስም ያሳደኩት ልጄ ተምሮልኝ ጥሩ ስራ ያዘልኝ ፡ በዚህ ደስ ብሎኝ ሳለ ልጄ በስራ ቦታ ካልሆኑ ልጆች ጋር ገጥሞ አዲስ ነገርን ተማረብኝ ፡ አንድ ቀን ማታ ሲመጣ “ እናቴ ሆይ ጌታን ተቀበይ” አለኝ ይህን ሲለኝ ደነገጥኩ “እመቤታችንስ” ስለው “ዙሪያ ጥምጥም መሄዱ ይበቃናል አንቺም እኔም ጌታን መቀበል አለብን” አለኝ ፡ እኔም ጧት ማታ አለቅስ ጀመር ፡ ለልጄም ይህ የነፍስ በሽታ ለስጋውም ተርፎ ሁለቱ ጆሮወቹ አልሰማም አሉት፡፡ በዚህም የተነሳ ጴንጤወች እንፀልይልህ ብለው በአዳራሻቸው ወሰዱት ፡ ጆሮወቼ ይድኑ ይሆን ብሎ ተስፋ ያደረገው ልጄም ይባስ ብሎ ሁለቱም አይኖቹ ጠፉ ፡ ከዚህ በኅላ እቤት ተኛ ፡ እኔም እያለቀስኩ እኖር ነበር፡፡ አስቡት ጆሮውንኳ ባይሰማ አይን ቢኖረው በምልክት እንግባባ ነበር ፡ ወይንም አይኑ ባይኖርና ጆሮው ቢሰማ በድምፅ እንግባባ ነበር አሁን ግን እጅግ ችግር ሆነብኝ፡፡ ከሁሉ የሚያስጨንቀኝ ግን እመቤቴን መክዳቱ ነበር፡፡ አንድ ቀን ቤተክርስቲያን ምስክርነት ሲሰጥ ሰምቼ እኔም በሃይላንድ ፀበል ይዜ ወደቤት ሄድኩኝ፡፡ በሁለቱ ጆሮወቹ ፀበሉን አፈሰስኩበት፡፡ የእመቤቴ ስእል ፊትም ተንበርክኬ “እመቤቴ ሆይ ጆሮውም አይስማ ፡ አይኑም አይይ ፡ ነገር ግን ልቡን መልሺልኝ” እያልኩ አልቅሼ ፀልየ ወደ መኝታየ ሄድኩኝ ሌሊት 10፡00 ላይ ልጄ “እማየ” ብሎ ጠራኝ እኔም “አቤት” አልኩት “ጆሮወቼ ሰሙልኝ” አለኝ፡፡ እኔም “ልብህ ቢሰማ ነውንጅ የሚሻለው” አልኩት፡፡ አሁንም ትንሽ ቆይቶ 11፡00 ላይ “ እማየ የእመቤታችንን ስእሏን ስጭኝ” አለኝ ፡ እኔም ሰጠሁት እሱም ስእሏን አቅፎ ለአንድ ሰአት ያክል አለቀሰ፡፡ ትንሽ ቆይቶም “እማየ” አለኝ ፡ እኔም “አቤት ልጄ” አልኩት ፡ እርሱም ”ሁለቱም አይኖቼ በሩልኝ” አለኝ፡፡ ደስታየን እንዴት እንደምገልፀው አላውቅም ፡ የኔ እመቤት የልጄን የነፍሱንም የስጋውንም ህመም ፈወሰችልኝ፡፡ አሁንም ልጄ እዚሁ ቤተክርስቲያን ከእመቤቴ ስእል ፊት ተንበርክኮ እየፀለየ ነው፡፡ እኔን የሰማች እናንተንም ትስማልኝ” ይህ ታአምር እንዴት ደስ ይላል፡፡ እመቤታችን ሆይ ስለዚህ እንወድሻለን ፡ ከፍ ከፍ እናደርግሻለን ፡ በልጅሽ አምነው በአማላጅነሽ ተማምነው ስምሽን የሚጠሩትን እንደማትተያቸው እናውቃለን፡፡ ድንግል ሆይ ስለዚህ ክብር ምስጋና ይገባሻል፡፡ አንቺን ለእናትነትና ለአማላጅነት የሰጠን ጌታችን አምላካችንና መድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የፍቅሩ ነገር ምን ይረቅ?
 ወስብሐት ለእግዚአብሔር ለዘበቅዱሳኒሁ ይሴባሕ ይእዜኒ ወዘልፈኒ ወለዓለም ዓለም አሜን፡፡ ወአሜን ለይኩን ለይኩን፡፡

Friday, April 12, 2013

መነኮስ አባ እንጦንዮስ




  • ምንጭ፡- የበረሃው ኮከብ ቅዱስ እንጦንዮስ መጽሐፍ

kiduse entonseጨለማ በዋጠው በግብፅ በረሃ ውስጥ ለብዙዎች አርዓያ በሆነ የእምነት ገድል የቅድስናን ብርሃን በማብራቱ የበረሃው ኮከብ ብለው ብዙዎች ይጠሩታል፡፡

ብፁዐዊ ቅዱስ እንጦንስ በምንኩስና ሕይወት ለመኖር ከጌታችን ከመድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በተማረው አብነታዊ ትምህርት (ማቴ.4፥1-10) ከዚህ ዓለም ተድላና ደስታ በመራቅ ከሰዎች ሁሉ ተለይቶ  ፍጹም መንፈሳዊ ተጋድሎን በመጋደል በተወለደ በ106 ዓመቱ ጥር 22 ቀን በ356 ዓ.ም. ከዚች ዓለም በሥጋ ተለይቷል፡፡ “ክቡር ሞቱ ለፃድቅ በቅድመ እግዚአብሔር” “የፃድቅ ሰው ሞቱ በእግዚአብሔር ፊት የከበረ ነው” በማለት ክቡር ዳዊት እንደተናገረው፣ “ቅድስት ቤተ ክርስቲያን የቅዱሳን የልደታቸውን ጊዜ፣ የተጋድሏቸውን ሁናቴ፣ ቃል ኪዳን የተቀበሉባቸውንና ያረፉባቸውን ዕለታት በክብር ታስባለች፡፡ ይህም በቅዱስ መጽሐፋችን “የፃድቅ መታሰቢያ ለበረከት ነው”(ምሳ.10÷7)፡፡ በመሆኑም “ስለ ፅድቅ የሚሰደዱ ብጹአን ናቸው ÷ መንግሥተ ሰማያት የእነርሱ ናትና” (ማቴ.5÷8) በሚለው በጌታችን ትምህርት የዚችን ዓለም ጣዕም ንቆ በምናኔ በመኖር ለመነኮሳት አብነት የሚሆናቸውን የቅዱስ እንጦንስን ዜና ሕይወት አቅርበናል፡፡ለመሆኑ ቅዱስ እንጦንስ ማን ነው? አስተዳደጉና የፈጸማቸው አገልግሎቶቹ ምን ይመስላሉ?

ልጅነት
እንጦንዮስ/እንጦንስ/ ትውልዱ ግብጻዊ ሲሆን ቤተሰቦቹም መልካሞችና ባለጸጎች ነበሩ፡፡ እነርሱም በሕፃንነት ኑሮው ከቤቱና ከወላጆቹ በስተቀር ምንም አላወቀም፡፡ እያደገና ዕድሜው እየጨመረ ሲሄድ ትምህርት ቤት አልገባም ነበር፡፡ ይህም ከሌሎች ልጆች ጋር ጓደኝነት ባለመፈለጉ ነበር፡፡ የእርሱ ፍላጎት በቅዱስ መጽሐፍ ተጠቅሶ እንደሚገኘው እንደ ያዕቆብ በብቸኝነትና በጭምትነት በቤቱ በመቀመጥ ቀላል ሕይወትን መምራት ነበር፡፡ ዘፍ.25፥27 በእርግጥ ከወላጆቹ ጋር ቤተ ክርስቲያን እየሄደ ያስቀድስ ነበር፡፡ በዚህም ከአንድ ልጅ ወይም ከአንድ ወጣት የሚታየው የመሰልቸትና የጥላቻ መንፈስ በጭራሽ አልታየበትም፡፡ ለወላጆቹ በመታዘዝ የሚሰጡትን ትምህርቶችና የሚነበቡትን ቅዱሳት መጻሕፍት በጥሞና ይከታተል ነበር፡፡ ከነዚህም የሚቀስመውን ጥቅም በልቡ በማስተዋል አኖረ፡፡ በሌላም በኩል በልጅነቱ ወራት ምንም እንኳ ያለ አንዳች ችግር ቢኖርም ወላጆቹን ለቅንጦትና ለድሎት ለምግብም ሲል አያስጨንቃቸውም ነበር፡፡ ይህን በመሰሉት ሁሉ አይደሰትም ነበር፡፡ በፊቱ በሚቀርብለት ብቻ ይረካ ነበር፡፡ ተጨማሪም አይጠይቅም፡፡

መጠራት
ወላጆቹ ከሞቱ በኂላ እንጦንዮስ ገና ልጅ ከነበረች አንዲት እኅቱ ጋር ብቻኛ ሆነ፡፡ በዚህ ወቅት ዕድሜው ከ18 እስከ 20 ዓመት ገደማ ነበር፡፡ ቤቱንና እኅቱንም ይጠብቅ ጀመር፡፡ እነርሱን ካጣ ከስድስት ወር በኋላ እንደ ልማዱ ወደ ቤተ ክርስቲያን ሲሄድ በመንገድ በኅሊናው ያስብ ጀመር፡፡

ሐዋርያት ሁሉን ትተው ጌታን እንደተከተሉት (ማቴ.10፣ 20፣19፣ 27)፤ በግብረ ሐዋርያት ሕዝቡ ያላችውን ሁሉ ሸጠው ለድሆች ይከፋፈል ዘንድ በሐዋርያት እግር ሥር ስለማኖራቸው (ሐዋ.4፡35)፤ ይህን ለመሳሰሉ ሥራዎች በሰማያት እንዴት ያለ ታላቅ ተስፋ እንዳላቸው (ኤፌ.1፡18 ቆላ.1፡15) እኒህን አሳቦች በኅሊናው እያወጣና እያወረደ ወደ ቤተ ክርስቲያን ገባ፡፡ በዚያም ወቅት ወንጌል ይነበብ ነበር፤ ሲያዳምጥ ጌታ በሀብታሙ ሰው የተናገረውን የሚጠቅሰው ምዕራፍ ተነበበ፡፡

“ልትጸድቅ ብትወድድ ሂደህ ያለህን ሁሉ ሽጥና ለድሆች ስጥ፡፡ መጥተህም ተከተለኝ፡፡ በሰማያት መዝገብ ታከማቻለህ፡፡” ማቴ.19፡21 ፡፡ እግዚአብሔር ቀድሞ ስለ ቅዱሳን እንዲያስብ እንዳደረገውና እዚህም የተነበበው በቀጥታ ለእርሱ እንደተነገረ ስለተሰማው እንጦንዮስ በቀጥታ ከቤተ ክርስቲያኑ በመውጣት ከዘመዶቹ የወረሰውን 300 ሄክታር ወይም 12 ጋሻ መሬት ለድሆች አከፋፈለ፡፡ መሬቱ ለምና ለዐይንም ያማረ ነበር፡፡ ይሁን እንጂ ለእርሱም ሆነ ለእኅቱ እንቅፋት እንዲሆንባቸው አልፈለገም፡፡ የተረፈውን ሁሉን ተንቀሳቃሽ ሀብቱን ሸጠ፡፡ አብዛኛውን ለድሃ ሰጥቶ ጥቂቱን ለእኅቱ አስቀመጠው፡፡

እንጦንዮስ በሌላ ቀን እንደገና ወደ ቤተ ክርስቲያን ገብቶ ሳለ ጌታ በወንጌል የተናገረውን ሲነበብ አደመጠ፡፡ “ለነገ አትጨነቁ” ይል ነበር ጥቅሱ ማቴ.6፡34፡፡ ይህንንም ሰምቶ ሳይዘገይ ወደ ቤቱ በመመለስ የተረፈውን ሁሉ ለድሆች ያከፋፍል ጀመር፡፡ እኅቱን ግን የታወቁና የታመኑ ወደሆኑ ደናግል ማኅበር ወሰዳት፡፡ በዚያም ታድግ ዘንድ ለደናግል ትቷት ተመለሰ፡፡ ከዚያ በኋላ ብቻውን በመሆኑ ንቁ ሆኖ ራሱን በመካድ በመኖሪያ ቤቱ አጠገብ ጊዜውን ለብሕትውና ሕይወት ሰጠው፡፡

ትሕትና
እንጦንዮስ ራሱን ዝቅ በማድረግና በነፍስ ትሕትና የጸና ነበር፡፡ ምንም እንኳ ታላቅና ዝነኛ ቢሆንም የቤተ ክርስቲያንን ልዑካንና ጸሐፍትን ከእርሱ ይልቅ እንዲከበሩ ይሻ ነበር፡፡ በጳጳሳትና በካህናት ፊት እራሱን ዝቅ አድርጎ እጅ ሲነሣ አሳፋሪ አያደርገውም፡፡ ዲያቆን ወደ እርሱ በመጣ ጊዜ ጠቃሚ ነጥብን ካገኘም ላገኘው ዕውቀት ሳያመሰግን አያልፍም፡፡

በገጽታው ሊገለጽ የማይቻልና ታላቅ የሆነ ብሩህ ገጽ ይነበብበታል፡፡ በመነኮሳት ጉባኤ ተቀምጦ ሳለ ቀድሞ የማይተዋወቀውን ሰው ሊያነጋግረው ከፈለገ ማንም ሳያመለክተው በዓይኖቹ እንደተሳበ ሁሉ ሌሎቹን አልፎ በቀጥታ ወደ እንጦንዮስ ይሄዳል፡፡ ከሌሎቹ ልዩ አድርጎ የሚያሳውቀው ቁመናው ምስሉ ሳይሆን የረጋ ባሕርይውና የነፍሱ ንጽሕና ነበር፡፡ ነፍሱ የማትነዋወጽ በመሆንዋ አፍአዊ ገጽታውም የረጋ ነበር፡፡ በመጽሐፍ  “ደስ ያለው ልብ ፊትን ያበራል፡፡ በልብ ኀዘን ግን ነፍስ ትሰበራለች፡፡”ተብሎ እንደተነገረው (ምሳ.15፥13)፡፡ ለምሳሌ ያዕቆብ አጎቱ ደባ ተንኮል እንዳሰበበት ባወቀ ጊዜ ለሚስቶቹ እንዲህ ብሏቸው ነበር የአባታችሁ ፊት ከእኔ ጋር እንደዱሮ እንዳልሆነ አያለሁ፡፡ ዘፍ.31፥5፡፡ ነቢዩ ሳሙኤል ዳዊትን ንጉሥ አድርጎ ይቀባው ዘንድ በተላከ ጊዜ ደስታን የሚያንጸባርቁ ዓይኖቹንና እንደ ወተት የነጡ ጥርሶቹን አይቶ አወቀው፡፡ 1ሳሙ.16፥10፡፡ እንጦንዮስም እንዲሁ ይታወቅ ነበር፡፡ አይነዋወጽም፡፡ ነፍሱ እርጋታ ነበራትና፡፡ አያዝንም፡፡ አዕምሮው ደስታን የተሞላ ነበር፡፡

ቅዱስ እንጦንዮስ ፍቅረ ነዋይ ላለቀቀው መነኩሴ ያስተማረው ትምህርት
ዓለመን ንቆ ገንዘብ ስለመውደድ ከመነኮሰ በኋላ ለድሆች ካከፋፈለ በኋላ ለራሱ ጥቂት ያስቀረ አንድ ወንድም ወደ ባሕታዊው ወደ እንጦንዮስ መጣ፡፡ እንጦንዮስም ይህን ካወቀ በኋላ እንዲህ አለው፡፡ “ መነኩሴ ለመሆን ከፈለግህ ወደ መንደር ሂድና ጥቂት ሥጋ ገዝተህ ራቁትህን በሰውነትህ ላይ ተሸክመህ ተመለስና ወደእኔ ና” አለው፡፡ያም ወንድም ይህን ባደረገ ጊዜ ወፎችና ውሾች በሰውነቱ እያንዣበቡ ይታገሉት ጀመር፡፡ በደረሰም ጊዜ እንጦንዮስ እንዳዘዘው ማድረጉን ጠየቀው፡፡ እርሱም የቆሰለውን ሰውነቱን ባሳየው ጊዜ እንጦንዮስ እንዲህ አለው፡-“ዓለምን ከናቁ በኋላ ገንዘብ የሚመኙትም እንደዚሁ በአጋንንት ይገደላሉ፡፡” አለው፡፡

ቅዱስ እንጦንስ ስለ ዕረፍቱ በቀደ መዛሙርቱ ፊት የተናገረው የመጨረሻ ንግግር
የአባቶቼን መንገድ እሄዳለሁ
እንደልማዱ መነኮሳትን ይጎበኝ ዘንድ በተራራው ውጭ ሳለ በጌታ ቸርነት አስቀድሞ ስለ ሞቱ ስላወቀ ለወንድሞች እንዲህ ሲል ተናገራቸው፡፡ “ይህ ከናንተ ጋር የማደርገው የመጨረሻው ግንኙነት ነው፡፡ በዚህም ሕይወት ዳግመኛ እንተያይ እንደሆነ እንጃ እጠራጠራለሁ፡፡ ዕድሜዬ አንድ መቶ አምስት ዓመት ገደማ ሆኗልና አሁን እኔ የምሞትበት ጊዜ ነው፡፡” ይህን በሰሙ ጊዜ ሽማግሌውን ሰው አቅፈው እየሳሙ ያለቅሱ ጀመር፡፡ እርሱ ግን ከውጭ ከተማ እንደሚለይ ሁሉ በደስታ ያወጋቸው ነበር፡፡ በጥብቅም መከራቸው፡፡ “ከጥረታችሁ ግዴለሽ አትሁኑ፡፡ በብሕትውና ሕይወት ፍጹም ተስፋ አትቁረጡ፡፡ ዕለት ዕለት እንደምትሞቱ ሆናችሁ ኑሩ፡፡ አስቀድሜ እንደተናገርኩት ነፍስን ከርኩስ አሳቦች ለመጠበቅ በሥራ ትጉ፡፡ ቅዱሳንን ምሰሉ፡፡ ቅድስና የሌለውን የስንፍና ትምህርታቸውን ታውቃላችሁና ወደ መለጣውያን (መናፍቃን) አትቅረቡ ኑፋቄያቸው ለማንም ግልጽ ነውና፡፡

በመጽሐፈ መነኮሳት (ፊልክስዮስ) መቅድም ላይ ስለ ቅዱስ እንጦንስ ከተፃፈው የሚከተለው ይገኛል፡-እንጦንዮስ (እንጦንስ) አባቱ ባለጸጋ ነበር፡፡ አገሩም ጽኢድ ዘአምፈለገ አቅብጣ ናት፡፡ …በሕጻንነቱ ከትምህርት ቤት ሄደ፡፡ ተምሮ ሲመለስ አባቱ “ሕግ ግባ” አለው፡፡ እርሱ ግን “አይሆንም” አለ፡፡ምነው ቢሉ ፈቃዱ እንደ ቀደሙ ሰዎች እንደ ኤልያስ፤ እንደ ኋላ ሰዎች እንደ ዮሐንስ ንጽሕ ጠብቆ፣ ከሴት ርቆ በድንግልና መኖር ነውና፤ ግድ አለው፡፡ “ግድማ ካልከኝ …ፍቀድልኝና ለእግዚአብሔር አመልክቼ ልምጣ እንጂ” አለ፡፡ “ደግ አመልክተህ ና” አለው፡፡ሄዶ ባቅራቢያው ካለ ዋሻ ገባ፡፡ ወዲያው አባትህ ታመመ አሉት፡፡ ቢሄድ አርፎ አገኘው፡፡ ገንዘቡን ሦስት ነገር አስቦ አስቀድሞ ይመጸውታል፡፡ መጀመሪያ ያባቴ በድኑ ከመቃብር ሳይከተት መብሉ በከርሰ ርሁባን፤ መጠጡ በጉርኤ ጽሙአን፤ ልብሱ በዘባነ ዕሩቃን ይከተት ብሎ፡፡ ሁለተኛው ወኢይወርድ ምስሌሁ ኩሉ ክብረ ቤቱ /ሀብቱ ንብረቱም ሁሉ አብሮ መቃብር አይወርድም/ ያለውን የነቢዩን ቃል ያውቃልና፤ ሦስተኛ የሚመንን ነውና ልብ እንዳይቀረው፡፡ ሲመጸውትም አየቴ ኀይልከ፤ አይቴ አእምሮትከ አይቴ ፍጥነትከ /ኀይልህ የት አለ እውቀትህስ የት አለ ፍጥነትህስ የት አለ/ እያለ መጽውቶታል፡፡ መጽውቶ አባቱን አስቀብሮ ሲያበቃ ቅዳሴ ለመስማት ከቤተክርስቲያን ገብቶ ቆመ፡፡ ቄሱ ወንጌል ብሎ ወጥቶ ሲያነብ እመሰ ፈቀድከ ትኩን ፍጹመ ሲጥ ኩሉ ንዋይከ ወሀብ ለነዳያነ ወነዓ ትልወኒ ያለውን ቃል ሰማ፡፡ ይህ አዋጅ የተነገረ ለኔ አይደለምን? ብሎ እኅት ነበረችው ከደብረ ደናግል አስጠግቶ ሂዶ ፊት ከነበረባት ዋሻ ገብቶ ተቀመጠ፡፡

ከዕለታት አንድ ቀን ወለተ አረሚ ሠናይተ ላህይ ይላታል ከደንገጡሮቿ ጋር በቀትር ጊዜ መጥታ ከዛፉ እግር ከውኃው ዳር አረፈች፡፡ ፊት እሷን አስጠጓት፤ ኋላ እርስበሳቸው ይተጣጠቡ ጀመር፡፡ እሱም እርቃናቸውን እንዳያይ ዓይነ ሥጋውን ወደ ምድር ዓይነ ነፍሱን ወደ ሰማይ አድርጎ ሲጸልይ ቆየ፡፡ ያበቃሉ ቢል የማያበቁለት ሆነ፡፡ ኋላ ደግሞ ቆይተው ነገረ ኀፊር እያነሱ ይጨዋወቱ ጀመር፡፡ ምነው እንግዲህማ አይበቃችሁም? አትሄዱም? አላቸው፡፡ ኦ እንጦኒ! ኦ እንጦኒ!፤ ለእመ ኮንከ መነኮሰ ሑር ኀበ ገዳም እንጦኒ ሆይ መነኩሴ እንደሆንክ ከዚህ ምን አስቀመጠህ ከበረሃ አትሄድም ነበርን?/ አለችው፡፡ ከዚያ አስቀድሞ መነኩሴ አልነበረ መነኮስ ማለት ከምን አምጥታ ተናገረች? ቢሉ ጌት ለአበው ትምህርት የሚሆነውን ነገር በማናቸውም ባልበቃ ሰው አድሮ መናገር ልማዱ ነው፡፡ አንድም እሱ ከመነኩሴ ፊት እንዲህ ያለ ኀፊር ትናገሪያለችን? አላት፡፡ ከሱ ሰምታ ኦ እንጦኒ ኦ እንጦኑ እመሰ ኮንከ መነኮሰ ሑር ሐበ ገዳም አለችው፡፡

እንጦኒ ኦ እንጦኒ እመሰ ኮንከ መነኮሰ ሑር ሐበ ገዳም እያለ ራሱን እየገሰጸ ፊቱን እየሰፋ ጽሕሙን እየነጨ ከዚያ ተነሥቶ አናብስት፤ አናምርት፤ አካይስት፤ አቃርብት ካሉበት ነቅዐ ማይ፤ ልምላሜ ዕፅ ከሌለበት ድሩክ ለተአቅቦ ይላል ዘር ተክል ከማይገኝበት ገዳመ አትፊር ሄደ፡፡ የዚህ መንገዱ ፍለጋ የለውም፡፡ አሸዋ ላሸዋ ነው፡፡ ነጋድያን ሲጓዙ የወደቀውን ያህያና የግመል ፋንድያ እያዩ በዚያ ምልክት ይሄዳሉ፡፡ በረሃነቱም ጽኑ ነው፡፡ ከሐሩሩ ጽናት የተነሣ በቀትር ጊዜ ከደንጊያ ላይ ተልባ ቢያሰጡ ይቆላል፡፡ እሱም ከዚያ ሄዶ ሲጋደል አጋንንት ጾር አነሱበት፡፡ ኦ ሕጹጸ መዋዕል እፎ ደፈርከ ዝየ፡፡ /በእድሜ ሕፃን የሆንክ ከዚህ እንደምን ደፍረህ መጣህ?/ አዳም ከወጣበት ገነት እንጂ እገባ ብሎ ነው፡፡ ብለው ዘበቱበት፤ እሱም በትሕትና ይዋጋቸዋል፡፡ መሆንማ ይሆን ብላችሁ ነውን? እናንተ ብዙ አኔ አንድ ብቻዬን፤ እናንተ ረቂቃን እኔ ግዙፍ፡፡ እናንተ ኀያላን እኔ ደካማ በኀይለ ክርስቶስ ብችላችሁ ነው እንጂ ያለዚያስ አልችላችሁም እያለ በትሕትና ሲዋጋቸው ኖረ፡፡

ከዕለታት ባንድ ቀን ይኸን ፆር አልቻልሁትም ልሂድ እንጂ ብሎ ሲያስብ አደረ፡፡ ማለዳ በትረ ሆሣዕና ነበረችው ያችን ይዞ ከደጃፉ ላይ ቆመ፡፡ እንዳይቀርም ፆሩ ትዝ እያለው እንዳይሄድም በዓቱ እየናፈቀው አንድ እግሩን ከውስጥ፤ አንድ እግሩን ከአፍአ አድርጎ ሲያወጣ ሲያወርድ መልአኩ የሰሌን ቆብ ደፍቶ፤ የሰሌን መቋረፊያ ለብሶ፤ የሰሌን መታጠቂያ ታጥቆ ብትን ሰሌን ይዞ መጣ፡፡ ምን ሊያደርግ ይሆን? ሲል ፊቱን ወደ ምሥራቅ መልሶ ቆመ፡፡ ወዲያው ጸሎተ ወንጌልን፤ ነአኩቶን፤ ተሠሀለኒን፤ ደግሞ መጀመሪያ ለሥላሴ እጅ ነሳ፡፡ ከዚያ በኋላ አንድ አቡነ ዘበሰማያት ሠላሳ ስድስት ሰጊድ አድርሶ በመጨረሻ አንድ ጊዜ እጅ ነሥቶ ተቀመጠ፡፡ ወዲያው ያን ብትን ሰሌን አቅርቦ ይታታ ጀመር፡፡ እንጦንዮስም እንግዲህማ የዚህን ፍጻሜ ሳላይ እሄዳለሁን? ብሎ ተቀምጦ ይመለከተው ጀመር፡፡ ሠለስት ሲሆን ደግሞ ተነሥቶ አቡነ ዘበሰማያቱንም ሰጊዱንም ያንኑ ያህል አደረሰው፡፡ የቀሩትንም የሰዓቱንም የሠርኩንም እንደዚሁ አድርጎ አሳየው፡፡ በሠርክ ኦ እንጦኒ ከመ ከመዝ ግበር ወለእመገበርከ ዘንቱ ትድኀን እምጸብአ አጋንንት አለው /እንጦኒ ሆይ እንደዚህ እንደዚህ ሥራ፤ ይህንን ከሠራህ ከአጋንንት ጠብ ትድናለህ/፡፡ ማለት ነው፡፡ የንዋሙን የመንፈቀ ሌሊቱን ግን እርሱ ጨምሮታል፡፡ ንዋም ጌታ የጸለየበት፤ ቀትር የተሰቀለበት፤ ሰዓት ነፍሱን ከሥጋው የለየበት፤ ሰርክ መቃብር የወረደበት ነውና ይህን ሁሉ አንድ አድርጎ ዳዊት ሰብአ ለዕለትየ እሴብሐከ ብሏል፡፡ /መዝ.118፥164/

ሠላሳ ዓመት ሲሞላው ጌታ በዕለተ ዓርብ የለበሰውን ልብስ አልብሶታል፡፡ ማየት ከመልአክ፤ መቀበል ከአምላክ እንዲሉ ይህም ምሳሌ ነው፡፡ ቆብ የአክሊለ ሦክ፤ ቀሚሱ የከለሜዳ፤ ቅናቱ የሀብል፤ ሥጋ ማርያም የሥጋ ማርያም፤ አስኬማ የሰውነት ወተመሰለነ በአስኬማሁ እንዲል፤እርሱም ይህን ተቀብሎ በዚህ ዓለም እኔ ብቻ ነኝን ሌላም አለ? ብሎ ወደ እግዚአብሔር አመለከተ፡፡ ጌታም አለ እንጂ አንድ ጊዜ ተራምዶ ሁለተኛውን ሳይደግም የሚሠራውን ሥራ ዓለሙ ሁሉ ቢሰበሰብ የማይሠራው፡፡ በጸሎቱ ዝናም የሚያዘንም ፀሐይ የሚያወጣ፤ እንደዚህ ያለ ወዳጅ አለኝ አለው፡፡ ይኸን ሰው ለማየት ልሂድን ልቅር? ቢለው ሂድ አለው፡፡ መልአኩ እየመራ አደረሰው፡፡ ጳውሎስ /ጳውሊ/ ከበዓቱ ወጥቶ ፀሐይ ሲሞቅ ነበር፡፡ ሲመጣ አይቶ ከበዓቱ ገብቶ ወወደየ ማእጾ ውስተ አፈ በዓቱ /ከበዓቱ አፍ ውስጥ መዝጊያ ጨመረ/ ይላል ዘጋበት፡፡ ከደጃፉ ቆሞ አውሎግሶን አውሎግሶን አለ፡፡ ስለ እግዚአብሔር ብለህ ክፈትልኝ ማለት ነው፡፡ ሰው እንደሆንክ ግባ ብሎ ከፈተለት፡፡ ገብቶ ማን ይሉሃል? አለው ስሜን ሳታውቅ እንደምንም መጣህ? አለው፡፡ እንጦንዮስም ፍጹም ነውና ቢጸልይ ወዲያው ተገልጾለት፤ ጎድጎድኩ ወተርህወ ሊተ ሀሰስኩ ወረከብኩ ጳውሎስ ገዳማዊ አለው፡፡

ጳውሎስ/ጳውሊ/ ትባላለህ ቢለው አደነቀ፡፡ ተጨዋውተው ሲያበቁ ባጠገቡ ለብቻው በዓት ሰጠው፡፡ እንጦንዮስም ከዚያ ሆኖ ጸሎቱን ሲያደርግ ዋለ፡፡ ወትሮ ለጳውሊ መንፈቀ /ግማሽ/ ኅብስት ይወርድለት የነበረ ማታ ምሉዕ ኅብስት ወረደለት፡፡ በፈቃደ እግዚአብሔር መምጣቱን ያን ጊዜ አወቀው፡፡ ወዲያው ያን ኅብስት ከሁለት ገምሶ እኩሌተውን ለራሱ አስቀርቶ እኩሌታውን ሰጠው፡፡ ያን ተመግበው ሌት ሁሉም በየሥራቸው ክብራቸው ተገልጾ ሲተያዩ አድረዋል፡፡ ጳውሎስ አሥር ጣቶቹን እንደ ፋና ሆነው እያበሩለት አራቱን ወንጌል ሲያደርስ እንጦንዮስም እንደ አምደ ብርሃን ተተክሎ ሲያበራ ተያይተዋል፡፡

በዚያች ሌሊት ከዚያ ቦታ ጨለማ ጠፍቶ አድሯል፡፡ በነጋው ሠለስት እላፊ ሲሆን ጸሎታቸውን አድርሰው ሲያበቁ ተገናኝተው ሲጨዋወቱ፤ እንጦንዮስ ያረገውን ቆብ አይቶ፤ ይህማ ከማን አገኘኸው? አለው፡፡ እርሱ ባለቤቱ ስጠኝ አለ፡፡ እርሱም የጌታን ቸርነት ያደንቅ ጀመር፡፡ እንጦንዮስም እስኪ በኔ ብቻ የሚቀር እንደሆነ ለሌላም የሚያልፍ እንደሆነ አመልክትልኝ አለው፡፡ አመለከተ፡፡ ወዲያው ተገለጸለት፡፡ ወአክሞሰሰ ይላል፡፡ ደስ አለው፡፡ ምን አየህ? ቢለው ጽዕድዋን አርጋብ /ነጫጭ ርግቦች/ በጠፈር መልተው አንተ እየመራሀቸው ተከትለውህ ሲሄዱ አየሁ አለው፡፡ ምንኑው ቢለው? እሊህማ በዚህ በቆቡ የምትወልዳቸው ንጹሐን ጻድቃን ልጆችህ ናቸው አለው፡፡  ሁለተኛ አመልክትልኝ አለው፡፡ አመለከተ ወደመነገጹ ይላል፡፡ አዘነ ምነው ቢሉ በክንፋቸው ጥቁር ተቀላቅሎባቸው አየሁ አለው፡፡ ምንድንናቸው ቢለው ጽድቅና ኀጢአት እየቀላቀሉ የሚሠሩ ልጆችህ ናቸው አለው፡፡ ሦስተኛ አመልክትልኝ አለው፡፡ አመለከተ ገአረ ወበከየ ይላል፡፡ ቃሉን ከፍ አድርጎ ጮኸ፡፡ ምነው አለው አርጋብስ አርጋብ ናቸው አለው፡፡ ነገር ግን በመጨረሻ ዘመን የሚነሡቱ እንደ ቁራ ጠቁረው አየሁዋቸው አለ፡፡ ምንድናቸው? ቢለው ሀሳሲያነ ሢመት /ሹመት ፈላጊዎች/፤ መፍቀሪያነ ንዋይ /ገንዘብ የሚወዱ/ እለ ይሠርኡ በነግህ ማዕደ ምስለ መኳንንት /ከመኳንንት ጋር በጥዋት ማዕድ የሚቀመጡ/ ይላቸዋል፡፡ በፍጻሜ ዘመን የሚነሡ ኀጥአን ልጆችህ ናቸው፡፡ አለው፡፡ ያለ ንስሓ ባይጠራቸው እስኪ አመልክትልኝ አለው፡፡ አመለከተ፡፡ የዚህ ምላሽ አልመጣለትም ይላሉ፡፡

ከዚህ በኋላ ጳውሊ እንግዲህ ይህን ከራስህ ያደረግኸውን ለኔ ስጠኝ ላንተ ሌላ ሠርተህ አድርግ አለው፡፡ ይህንንስ እንዳልሰጥህ ከባለቤቱ ተቀብዬዋለሁ፡፡ ነገር ግን ሥራውን ለምጄዋለሁ ሌላ ሠርቼ ላምጣልህ አለው፡፡ እንዲያስ አትዘግይ ቶሎ ሠርተህ አምጣልኝ አለው፡፡ ጊዜው እንደደረሰ አውቆታልና ይላሉ፡፡ እንጦንስም ሠርቶ ይዞ ሲመጣ ጳውሊ አርፎ ነፍሱን መላእክተ ብርሃን ይዘዋት ሲያርጉ አየ፡፡ ማነው ብሎ ጠየቃቸው፡፡ ያ ሰው አርፏልና ሂደህ ቅበረው አሉት ይህንሳ የያዝኩትን ቆብ ልተወውን? አላቸው፡፡ አትተው አድርግለት ብለውታል፡፡ ከምንኩስና አስቀድሞ የሠሩትን ሥራ ከንቱ እንዳይደለ ለማጠየቅ ነው፡፡

ቢሄድ መጽሐፉን ታቅፎ፤ አጽፉን ተጎናጽፎ፤ ከበዓቱ አርፎ፤ አገኘው፡፡ ከራስጌው ቆሞ ሲያለቅስ ሁለት አናብስት መጡ፡፡ የመቃብሩን ነገር እንደምን ላድርግ ነኝ አያለ ሲጨነቅ በእጃቸው እንደመጥቀስ አድርገው አሳዩት፡፡ ልኩን ለክቶ ሰጣቸው፡፡ ቆፈሩለት እሱን ቀብሮ እንግዲህ ከዚህ እኖራለሁ ብሎ አሰበ፡፡ ጌታ ግን ዛሬ በሱ ቦታ ላይ ሌላ ሰው አላየበትምና አይሆንልህም ሂድ አለው፡፡ አጽፉንና መጽሐፉን ይዞ ሂዶ እስክንደርያ ሲደርስ ሊቀ ጳጳሱ አትናቴዎስ ወዴት ሄደህ ነበር? አለው፡፡ እንዲህ ያለ ሰው ልጠይቅ ሄጄ ነበር፡፡ አርፎ አግኝቼ ቀብሬው መጣሁ፡፡ አለ፡፡ ልሄድና ከዚያ ልኑር? አለው አይሆንልህም አትሂድ እኔም አስቤ ነበር፡፡ የማይሆንልኝ ሆኖ መጣሁ እንጂ አለው፡፡ ባይሆን ለበረከት ያህል አጽፊቱን ጥለህልኝ ሂድ ብሎ ትቶለት ሄደ፡፡ መዓርግ ሲሰጥ ሥጋውን ደሙን ሲለውጥ በውስጥ ያቺን ይለብስ ነበር፡፡

ከዚያ በኋላ በዚህ ቆብ እንጦንዮስ መቃርስን፤ መቃርስ ጳኩሚስን፤ ጳኩሚስ ጳላሞንን፤ ጳላሞን ቴዎድሮስ ሮማዊውን ቴዎድሮስ ሮማዊ አቡነ አረጋዊንና አባ ዳንኤልን ይወልዳል፡፡ አባ ዳንኤል አቡነ አውስጣቴዎስ፤ አቡነ አረጋዊ እስከ አቡነ ተክለሃይማኖት ያሉትን ወልደዋል፡፡ ከዚህ በኋላ መነኮሳቱ እንደ ሳር እንደ ቅጠል በዝተው ተነሥተዋል፡፡ ይሩማሊስ፤ ጳላድዮስ የሚባሉ ሁለት ሊቃውንት መነኮሳት ከግብፅ ተነሥተው አገር ላገር እየዞሩ የአበውን ዜና በሕይወት ያሉትን ከቃላቸው የሞቱትን ከአርድአቶቻቸው እየጠየቁ ቃለ አበው፣ ዜና አበው እያሉ ጽፈዋል፡፡
         ምንጭ፡- የበረሃው ኮከብ ቅዱስ እንጦንዮስ መጽሐፍ