Wednesday, November 21, 2012

ነገረ ማርያም በብሉይ ኪዳን

                                                          ምዕራፍ አንድ
                               ነገረ ማርያም ከኦሪት ዘፍጥረት እስከ ኦሪት ዘዳግም
                                                          ክፍል አንድ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን    
ታቦት ዘዶር: የአምላክ ታቦት (ማደሪያ) የሆነች ቅድስት ድንግል ማርያም በኢየሩሳሌም ሰማያዊት በምትገኘው ታቦት ትመሰላለች::እግዚአብሄር አምላክ በዚህች በእለተ እሁድ ከፈጠራቸው ከሰባቱ ሰማየት አንዷ በመንበረ መንግስት አንፃር ያለችው ኢየሩሳሌም ሰማያዊት ትገኛለች (ገላትያስ 4*26 : ዕብራውያን 12*12)ይህቺውም ሰማይ እንደ ቤተመቅደስ አራት ማእዘን ያላት ስትሆን አስራ ሁለት ደጃፎች አሏት !! በዚያም የብርሃን አዕማድ ደግፎ የብርሃን ክዳን ከፍክፎ ዙሪያዋን በክዋክብት አምሳል የብርሃን መርገፍ አዙሮባታል::
     ዮሃንስ ወንጌላዊው ስለ ኢየሩሳሌም ሰማያዊት ነገር በራእዩ ላይ <<የእግዚአብሄር ክብር ያለባትን ቅድስቲቱን ከተማ ኢየሩሳሌምን ከሰማይ ከእግዚአብሄር ዘንድ ስትወርድ አሳየኝ ብርሃንዋም እጅግ እንደከበረ ድንጋይ እንደ ኢያስጲድ ድንጋይ ሆኖ እንደ ብርሌ የጠራ ነበር ታላቅና ራዥም ቅጥር ነበራት አስራ ሁለት ደጆች ነበሯት >> (ራእይ 21*11-12)በማለት ተናግሮላታል::
     በዚህች በሰማያዊቲየርሳሌም ጌታ ወርዷ ቁመቷ የትስተካከለ የብርሃን ፅላት ቀርፆ በውስጧ አኑራል( ራእይ11*19):: ይህቺውም ታቦት ዘዶር ተብላ ትጠራለች ሊቁ ኤጲፋኒዮስ የሥነ ፍጥረትን ነገር በሚናገረው መጽሀፍ << ወውስቴታ ታቦት ዘዶር ዘያበርህ በጸዳለ ሥሉስ ቅዱስ >> (በስላሴ ጸዳልየሚያበራ ታቦት ዘዶር በውስጧ በኢየሩሳሌም ሰማያዊት አለ በማለት የተናገረላት ይህች በኢየሩሳሌም ሰማያዊት ያለችው ታቦት ዘዶር የአማናዊት ታቦት የሥላሴ ማደሪያ የሆነችው በምድረ ኢየሩሳሌም የተገኘችው የቅድስት ድንግል ማርያም ምሳሌ ናት::
     ይኸውም መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ከእግዚአብሄር ዘንድ ትልኮ ቅድስት ድንግል ማርያምን የአምላክ ታቦት (ማደሪያ) መሆኗን <<መንፈስ ቅዱስ በአንቺ ላይ ይመጣል የልዑል ኅይል ይጸልልሻል ስለዚህ ደግሞ ከአንቺ የሚወለደው ቅዱስ የእግዚአብሄር ልጅ ይባላል >> (ሉቃስ 1*35) በማለት አጉልቶ መስክሮላታል:: ይህንን ምስጢር በጥልቀት የተረዳ አባ ሕርያቆስም በቅዳሴ ማርያም መጽሀፉ << ወውስቴታ ታቦት ዘዶር እንተ ይእቲ እግዝትነ ማርያም>> (ከእነርሱም ጋራ ታብይ ዘዶር ወዳለችበት ያግባችሁ ይህቺውም እመቤታችን ማርያም ናት :; በማለት ታቦት ዘዶር የእውነተኛይቱ የአምላክ ታቦት የድንግልማርያም ምሳሌ መሆናን አጉልቶ ገልጾታል::
ይቆየን
የቅድስት ድንግል ድንግል ማርያም አማላጅነት
 የሰባቱ ሊቃነ መላእክት የቅዱሳን የሰማእታት የቅዱሳን አባቶች ተራዳኢነት አይለየን 
ወስብሐት ለእግዚአብሔር ለዘበቅዱሳኒሁ ይሴባሕ ይእዜኒ ወዘልፈኒ ወለዓለም ዓለም አሜን፡፡ ወአሜን ለይኩን ለይኩን፡፡

መጋቤ ሐዲስ ሮዳስ 2002ዓ/ም

No comments:

Post a Comment